በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል በ2017 በጀት ዓመት በተያዘለት የመንግስት በጀት ለሆስፒታሉ መገልገያ የሚሆኑ የህክምና መርጃ መሳሪያ ግዥ፣ የፅዳት አገልግሎት ግዥ የኢፖክሲ ስራ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የግልጽ ጨረታ ቁጥር 06/ 2017
በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል በ2017 በጀት ዓመት በተያዘለት የመንግስት በጀት ለሆስፒታሉ መገልገያ የሚሆኑ የህክምና መርጃ መሳሪያ ግዥ፣ የፅዳት አገልግሎት ግዥ የኢፖክሲ ስራ ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች
- የዘመኑን ግብር ከፍለው በመስኩ የታደሰ ሕጋዊ ፈቃድ ያላቸው የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆናቸውና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው የዋና ምዝገባ ሰርተፍኬት እንዲሁም በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ ስለመሆናቸው የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ከላይ የተዘረዘሩ የእቃ ወይም አገልግሎት አይነቶች በሙሉ ወይም በከፊል መጫረት የሚችሉ ሲሆን ለእያንዳንዱ ሎት (የጨረታ ሰነድ) የማይመለስ ብር 300.00 (ሦስት መቶ ብር) በመክፈል ጨረታው በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ በሆስፒታሉ ፋይናንንስ ዳይሬክቶሬት ቢሮ ድረስ በአካል በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ
- የህክምና መሳሪያ ግዥ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/
- የፅዳት አገልግሎት ግዥ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/
- የኢፖክሲ ስራ ግዥ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/
በባንክ በተረጋገጠ CPO ለጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል ተብሎ በማዘጋጀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚጫረቱበትን ዋጋ በጨረታ ሰነዱ ውስጥ በተዘጋጀው ዋጋ ማቅረቢያ ሰንጠረዥ ላይ ብቻ በመሙላት የድርጅታቸውን ማህተምና ፊርማ አኑረው ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ለእያንዳንዳቸው ኦርጅናልና ኮፒ በማድረግ 4 (አራት ፖስታ) በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ዘወትር በስራ ቀንና ሰአት ከጠዋቱ 2፡30- 11፡30 ሰዓት ድረስ ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው የጨረታ ሳጥኑ ከታሸገ በኋላ የሚቀርብ የመጫረቻ ሰነድ ተቀባይነት አይኖረውም።
- ጨረታው በ11ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዛው እለት ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሆስፒታሉ አዳራሽ ውስጥ ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች በራሳቸው ፈቃድ ባይገኙ ጨረታው ከመከፈት አያግደውም፡፡ 11ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን ይከፈታል።
- ተጫራቾች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ባቀረቡት የመወዳደሪያ ሃሳብ ላይ ለውጥ ወይም ማሻሻያ ማድረግና ከጨረታው ራሳቸውን ማግለል እንዲሁም ሌላ ተጫራች በሰጠው ዋጋ ላይ ተንተርሶ ዋጋ ማቅረብ አይችሉም::
- አሸናፊ ተጫራች አሸናፊ የሆነባቸውን እቃዎች ያለምንም አቅርቦት ችግር አስተማማኝ የሆነ የእቃ ክምችት ያለውና የእቃውን ጠቅላላ ዋጋ 10% ለውል ማስከበሪያነት አስይዞ ተገቢውን ውል በመፈጸም እቃዎቹን በሆስፒታሉ ግቢ ንብረት ክፍል ድረስ በማምጣት ገቢ ማድረግ አለበት፡፡
- ሆስፒታሉ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ /በከፊል/ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ ፡- አቃቂ ቃሊቲ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ወይም ልዩ ስሙ ጥምቀተ ባህር ወይም አቃቂ መሿለኪያ ፊት ለፊት
ለበለጠ መረጃ - ስልክ ቁጥር፡- 0910248522 በስራ ሰአት መደወል ይችላል፡፡
የጥሩነሽ ቤጂንግ አጠቃላይ ሆስፒታል
