አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከላይ የተጠቀሰውን ብዛታቸው 12 የሚሆኑ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የሽያጭ ጨረታ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር፡-AAU/NCB/pd/05/2017/25
ያገለገሉ ተሽከርካሪዎች ሽያጭ ጨረታ
-
- አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ከላይ የተጠቀሰውን ብዛታቸው 12 የሚሆኑ ያገለገሉ ተሽከርካሪዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
- ተሽርካሪዎቹ የሚገኙበት አድራሻ 6 ኪሎ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የትራንስፖርትና ተሽከርካሪ ጥገና ክፍል ሲሆን ለመግዛት ፍላጎትና ብቃት ያላቸው ተጫራቾች በታሸገ ኤንቨሎፕ የጨረታ ሰነድ ለአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ እንድታቀርቡ ተጋብዛችኋል፡፡
- ጨረታው በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግዥና ንብረት አስተዳደር መመሪያ ሥነ-ሥርዓት መሰረት ይፈፀማል::
- ፍላጎት ያላቸው ተጫራቾች ከዚህ በታች በተራ ቁጥር 7 (ሀ) በተገለፀው አድራሻ የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 400.00 (አራት መቶ ብር) በዩኒቨርሲቲው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አካውንት ቁጥር 1000087392067 ገቢ በማድረግና ደረሰኙን ይዘው በመቅረብ ስለተሽከርካሪዎቹ ሙሉ ዝርዝር የያዘውን ሰነድ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ከዚህ በታች በተራቁጥር 7 (ለ) በተገለጸው አድራሻ እስከ ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ ጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡ የጨረታ ማስከበሪያውን በተጫራቾች መመሪያ በተዘረዘረው መሰረት አያይዘው ያቀርባሉ፡፡ ዘግይተው የሚቀርቡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም። ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በቁጥር 7 (ሐ) በተጠቀሰው አድራሻ ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት 4፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች ከዚህ በታች በተራ ቁጥር 7 (ለ) በተገለጸው አድራሻ ሚያዝያ 16 ቀን 2017 ዓ.ም ጠዋት 4፡00 ሰዓት ወይም በፊት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ የጨረታ ሰነዱን በማስገባት በግዥ እና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ከጨረታ መክፈቻ ጊዜ በፊት ማቅረብ አለባቸው፡፡ ተጋባዥ ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ለአንድ ተሽከርካሪ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ባልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በዩኒቨርሲቲው ስም አሰርተው አያይዘው ማቅረብ አለባቸው። በተጨማሪም ጨረታው ከተከፈተ በኋላ ማንኛውም ተጫራች ከውድድሩ ከወጣ የተያዘው የጨረታ ማስከበሪያ የሚወረስ ይሆናል፡፡
- ሀ/ ሰነዶቹ የሚሸጡበት አድራሻ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ግዥ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 312
- ለ/ የጨረታው ሰነድ የሚገባበት አድራሻ አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 200
- ሐ/ ጨረታው የሚከፈትበት አድራሻ አዲስ አባባ ዩኒቨርሲቲ የቀድሞ ግዥና ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ ቁጥር 200
- የጨረታ አሸናፊው ድርጅት የውል ስምምነት ከተፈረመበት ቀን በኋላ ባሉት 10 ቀናት ውስጥ ለየኒቨርሲቲው ሙሉ ክፍያ በመፈጸም ከከፈለበት ቀን ጀምሮ ባሉት በ10 ተከታታይ ቀናት ውስጥ እቃውን ማንሳት አለበት፡፡
- ዩኒቨርሲቲው በከፊልም ሆነ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብት አለው፡፡
ስልክ ቁጥር 011-122-00 01/011-124-32-72 ፖ.ሣ.ቁ 1176
አዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የግዥና ንብረት አስተዳደር ቢሮ
