የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ እያስተዳደረው ያለው የወልቂጤ ስታዲዮም ውስን የጥገና ስራዎች ለማከናወን የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 8/2017
የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለጉራጌ ዞን ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ እያስተዳደረው ያለው የወልቂጤ ስታዲዮም ውስን የጥገና ስራዎች ለማከናወን የግንባታ ፈቃድ ያላቸው ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው መወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ማሟላት ይኖርባቸዋል፤
- ደረጃቸው ጂሲ5 እና ከዚያ በላይ ፈቃድ ያላቸው መሆን አለባቸው::
- የዘመኑን የንግድ ፈቃድ ያደሱ ሆነው ዋናውንና ኮፒውን ማቅረብ የሚችሉ፣
- የዘመኑን የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እና የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፤
- በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የሚገዙትን የጨረታ ሰነድ ጠቅሰው በማመልከቻ ሲጠይቁ ተወካዮች ከሆኑ ከድርጅቱ ህጋዊ ውክልና ይዘው መቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ድረስ የማይመለስ ብር 500 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል ከጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታውን ቴክኒካልና ፋይናንሻል ዶክመንት ሲያቀርቡ፡-
ሀ/ ለቴክኒካል ዶክመንት አንድ ኦሪጅናል እና ሁለት ፎቶ ግራፊክ ኮፒዎች እያንዳንዳቸውን በሰም በማሸግ ሁሉንም በአንድ ትልቅ እናት ፖስታ በማሸግ የጨረታ ማስከበሪያ 100,000 /አንድ መቶ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ፣ ወይም ቢድ ቦንድ ከሆነ ለ120 /ለአንድ መቶ ሃያ ቀን/ የሚቆይ ቢድ ቦንድ ከኦሪጅናል ቴክኒካል ዶክመንት ጋር በማድረግ /ቴክኒካል በሚል በመለየት/፤
ለ/ ለፋይናንሻል ዶክመንት አንድ ኦሪጅናልና ሁለት ፎቶ ግራፊክ ኮፒ በሰም በማሸግ /ሁሉንም በአንድ ትልቅ እናት ፖስታ ውስጥ በማሸግ/ ፋይናንሻል በሚል በመለየት እስከ 21ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት አለባቸው፣
- የጨረታው ማስከበሪያ ሲፒኦ በጉራጌ ዞን ፋ/ኢ/ል መምሪያ ስም መሰራት አለበት፡፡
- ከተራ ቁጥር 1-7 የተጠቀሱትን መስፈርቶች ሙሉ ለሙሉ ያላሟላ ተጫራች ከውድድር ውጪ ይሆናል፡፡
- የጨረታው ቴክኒካል ዶክመንት በ21ኛው ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- የፋይናንሻል /የፕሮጀከቱ ግንባታ ዋጋ/ ከቴክኒክ ግምገማ ውጤት በኋላ የቴክኒክ ግምገማውን ያለፉት ተጫራቾች ሰነድ ብቻ የጨረታ ኮሚቴው በማስታወቂያ በሚገልፀው ቀን ይከፈታል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው::
ማሳሰቢያ፡-
- በአፈፃፀም ምከንያት ለሶስት ዙር ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው መወዳደር አይችሉም፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ ወደሚቀጥለው የሥራ ቀን ይተላለፋል፡፡
- በጨረታው ሂደት ውስጥ ተሻሽሎ የወጣው የክልሉ የግዢ መመሪያ ተግባራዊ እንደሚደረግ እንገልጻለን።
ለበለጠ መረጃ፡- 0113300112
የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
ወልቂጤ
