የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የሞጆ ሎጅስቲክስ ማዕከል ከሞጆ አዳማ ሰራተኞችን የሚያመላልስ ሰርቪስ መኪና በጨረታ አወዳድሮ በኮንትራት ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ለመጀመሪያ ጊዜ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር-ESLSE/P&T/REQ/2025/35070
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጅስቲክስ የሞጆ ሎጅስቲክስ ማዕከል ከሞጆ አዳማ ሰራተኞችን የሚያመላልስ ሰርቪስ መኪና በጨረታ አወዳድሮ በኮንትራት ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ሎት-አስራ ሶስት፡- የሰርቪስ መኪና ኪራይ ጨረታ ግዥ
በዚህ መሰረት፡-
- በዘርፉ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የቫት የምስክር ወረቀት፣ የዘመኑን ግብር የከፈሉ ለመሆናቸው የሚያሳይ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ደረጃውን የጠበቀ ሰርቪስ መኪና ማቅረብ የሚችሉ፣
- 45 ሰዎችን መጫን የሚችል ሰርቪስ መኪና፣
- ንጽህናውን የጠበቀ ሰርቪስ መኪና ማቅረብ የሚችል፣
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን ሞልቶ የሚመልሰው በድርጅቱ ድረ ገጽ (WWW.ESLSE.COM) ላይ በERP SYSTEM በዋና መ/ቤት ምዝገባ ካካሄዱ በኋላ ብቻ (ከዚህ ቀደም ያልተመዘገቡ ከሆነ) በሚሰጣቸው መለያ ቁጥር መሰረት የሚሞሉ መሆኑን እናሳውቃለን፡፡
- የጨረታው መክፈቻ እና መዝጊያ ጊዜ ሲስተሙ ላይ በሚወጣው ሰዓት ይሆናል።
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ማስከበሪያ 10,000 (አስር ሺ ብር) በንግድ ባንክ ፣ በህብረት ባንክ ወይንም በኦሮሚያ ህ/ስራ ባንክ ብቻ ጨረታው ከመዘጋቱ በፊት ማስገባት ይኖርበታል፡፡
- ቅ/ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ ማብራሪያ፡- በስልከ ቁጥር 0221162194 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ የባህር ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ
ሞጆ ሎጀስቲክስ ማዕከል
