Tender Detail

Tender Details


የጢስ እሳት ውሃ ስራዎች ኃ/የተ/የግ/ማህበር ከታች የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ከአቅራቢዎች ለመግዛት ይፈልጋል።


 

የጨረታ ስታወቂያ

 

የጢስ እሳት ውሃ ስራዎች /የተ/የግ/ማህበር ከታች የተዘረዘሩትን እቃዎች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ከአቅራቢዎች ለመግዛት ይፈልጋል።

 

.

ሎት

የእቃው አይነት

የጨረታ ማስከበሪያ

የማቅረቢያ ጊዜ

1

ሎት 1

ስቲል ኬዚንግ (steel casing) አቅርቦት

100,000.00

ከስቶክ

2

ሎት 2

ኤሌክትሮ ሜካኒካል እቃዎች አቅርቦት

50,000.00

45 ቀናት

3

ሎት 3

Flor standing digital signage

30,000.00

45 ቀናት

 

ስለዚህ ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራና በጨረታው መሳተፍ የሚፈልግ አቅራቢ ድርጅት ዝርዝር የጨረታ ሰነዱን ከድርጅታችን ድረ-ገጽ www.tisisat.com ማግኘት ይችላል።

የተጫራቾች መመሪያ

  1. ተጫራቾች የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ የንግድ ፈቃድ የንግድ ምዝገባ የምስ ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና TIN ሰርተፍኬት፤ በዘርፉ ለመሰማራት የተሰጣቸውን ፈቃድ እና ተያያዥነት ያላቸውን የመልካም ስራ አፈፃፀም ማስረጃዎች ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
  2. ጨረታው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 15ኛው ቀን ከቀኑ 9:00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከቀኑ 930 ሰዓት ባህርዳር ከተማ አባይ ማዶ ቴዲ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ጎን በሚገኘው ዋናው /ቤት ተጫራቾች እና ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል፡፡
  3. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ከድርጅታችን ድረ-ገጽ www.tisisat.com ማግኘት ይችላሉ።
  4. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ በሰንጠረዥ የተመለከተውን ገንዘብ CPO ወይም ያለቅድመ ሁኔታ እንደተጠየቀ ለገዥ የሚከፈል (Unconditional Bank Guarantee) ማስያዝ አለባቸው፡፡
  5. ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸውን እና ቴክኒካል ሰነዳቸውን ለየብቻ በተለያየ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራች ድርጅቶች ለሚያቀርቡት ዋጋ ለእያንዳንዱን እቃ ነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ በትክክ ሞልተው በግልፅ ማስቀመጥ አለባቸው::
  6. ይህ ጨረታ በኩባንያችን የግዥ መመሪያ PR-02/2013 መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡
  7. ኩባንያው በጨረታ ሰነዱ ላይ ከተገለፀው መጠን 25% ቢጨምር ወይም ቢቀንስ የጨረታ አሸናፊው ውል የመያዝ ግዴታ ይኖርበታል፡፡
  8. የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ 10 ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋውን 10% የውል ማስከበሪያ ያለቅድመ ሁኔታ ለገዥ የሚከፈል (Unconditional Bank Guarantee) በማሰራት ውል የመያዝ ግዴታ ይኖርበታል፡፡
  9. የማቅረቢያ ጊዜ ከላይ በሰንጠረዥ በተገለጸው መሰረት መሆን አለበት፡፡ የአቅራቢዎች ዋጋ ቢያንስ 90 ቀናት ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ፀንቶ መቆየት አለበት፡፡
  10. ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ በዚህ ጨረታ አይገደድም ወይም ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
  11. ማሳሰቢያ፤ ውድድሩ የሚካሄደው እንደ ኩባንያው ፍላጎች በሎት ወይንም በእያንዳንዷ እቃ ነጠላ ዋጋ በሚሞሉት ዋጋ መሰረት ይሆናል፡፡
  • ለበለጠ መረጃ በስልከ ቁጥራችን 058-220-48-26 /0583202548/ በፋክስ ቁጥራችን 0582204830 ይጠቀሙ፡፡

 

የጢስ እሳት ውሃ ስራዎች /የተ/የግ/ማህበር

 

Save Tender