ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የተገለጸውን የአስፓልት ፕላንት ገጠማ ፣ ተከላ እና የተሳካ ሙከራ ለማስደረግ በዘርፉ ፈቃድ ካላቸው ድርጅቶች በጨረታ አወዳድሮ ማስራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የተገለጸውን የአስፓልት ፕላንት ገጠማ ፣ ተከላ እና የተሳካ ሙከራ ለማስደረግ በዘርፉ ፈቃድ ካላቸው ድርጅቶች በጨረታ አወዳድሮ ማስራት ይፈልጋል፡፡
|
ተ.ቁ |
የማሽኑ አይነት |
የማሽኑ ሞዴል |
መለኪያ |
ብዛት |
የሚተከልበት ቦታ |
|
1 |
የአስፖልት ፕላንት |
Speco Asphalt Plant (TSAP-1500) |
በቁጥር |
01 |
ወልድያ ከተማ |
ስለዚህ ከዚህ በታች የተገለፁትን የጨረታ መወዳደሪያ መስፈርቶችን የሚያሟላ ማንኛውም አቅራቢ ድርጅት በጨረታው መወዳደር ይችላል፡፡
-
-
-
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፤ የንግድ ፈቃድ የምስክር ወረቀት፤ የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሰርተፊኬት ቁጥር (TIN) እና የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ የምስክር ወረቀት (VAT) ያላቸው መሆን አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚውል ሲፒአ ወይም ያለቅድመ ሁኔታ እንደተጠየቀ የሚከፈል ባንክ ጋራንቲ የተ.እ.ታክስን ጨምሮ ለሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር ብቻ) በኮርፖሬሽናችን ስም ማለትም ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን (Hibir Construction Corporation) ለ90 ቀናት ፀንቶ የሚቆይ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች በተራ ቁጥር 1 የተዘረዘሩትን የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ በማድረግ ከመጫረቻ እንዲሁም የጨረታ ማስከበሪያው የፋይናንሻል ፖስታ ዋና (ኦርጅናል) ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ መወዳደሪያ ሃሳባቸውን ፋይናንሻል ፖስታ ኮፒ (ቅጅ) እና ኦሪጅናል (ዋና) በማለት በተለያየ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታውን ዝርዝር መግለጫ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት የሚችሉ ሲሆን ሰነዱን የማይመለስ ብር 200.00 /ሁለት መቶ ብር ብቻ/ በመክፈል ከኮርፖሬሽናችን ፋይናንስ የስራ ሂደት ቢሮ ቁጥር 23 መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡበትን ዋጋ እና የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ማለትም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 20 (ሃያ ቀናት) ተከታታይ ቀናት ውስጥ ባሕር ዳር ከተማ ከሚገኘው አማራ ፓይፕ ፋብሪካ ፊት ለፊት ዋና መ/ቤታችን ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ዋናው መ/ቤት ግዥ ቢሮ በመቅረብ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው በ20ኛ ቀን በ4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን በ4፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡
- ኮርፖሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 058-3-20-35-76 መደወል ይችላሉ፡፡
-
-
ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
