Tender Detail

Tender Details

  • Company ነባር አጠቃላይ ንግድ አክሲዮን ማህበር
  • Address ኢትዯጵያ, Phone: 09-11-24-63-12
  • Website
  • Deadline30 Apr 2025, 12:00 AM
  • magazine
  • Bid Document Price
  • opening date2025-04-30 00:00:00
  • Categories Steel, Metals And Aluminium , Used Items

የነባር አጠቃላይ ንግድ አክሲዮን ማህበር ጥቅምት 11 ቀን 2017 ዓ.ም በህንፃው ላይ በደረሰው የእሳት ቃጠሎ ምክንያት ህንፃውን ወደ ነበረበት ለመመለስ ያመች ዘንድ ከቃጠሎ የተረፉ የተለያዩ ዓይነት ብረቶች እና አልሙኒየም በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡


 

የብረታ ብረት ሽያጭ የጨረታ ማስታወቂያ

 

የነባር አጠቃላይ ንግድ ሲዮን ማህበር ጥቅምት 11 ቀን 2017 . በህንፃው ላይ በደረሰው የእሳት ቃጠሎ ምክንያት ህንፃውን ወደ ነበረበት ለመመለስ ያመች ዘንድ ከቃጠሎ የተረፉ የተለያዩ ዓይነት ብረቶች እና አልሙኒየም በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራቾች የንግድ ፈቃድ እና የዘመኑን ግብር የከፈሉበትን ማስረጃ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡ ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ቀናት በአቅራቢያቸው ከሚገኝ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ) በሂሳብ ቁጥር 1000184750507 ገቢ በማድረግ ገቢ ያደረጉበትን የባን የገቢ ደረሰኝ በመያዝ ነባር አጠቃላይ ንግድ አክሲዮን ማህበር ሕንፃ ላይ 2 ፎቅ በሚገኘው ጊዜያዊ ቢሮ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የጨረታ ሰነዱን ማግኘት ይችላሉ፡፡

ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ብር 100,000.00 (አንድ መቶ ሺህ)

ከጨረታ ሰነዱ ጋር ያይዘው ማቅረብ አለባቸው::

ተጫራቾች የተለያዩ ዓይነት ብረቶችን እና አልሙኒየሞችን የሚገዙበትን የአንድ ኪሎ ግራም የመግዥያ ዋጋ በመሙላት በሰም በታሸገ ፖስታ በማሸግ ስምና ፊርማ በማድረግ ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡ አሸናፊው ተጫራች ውድድሩን ማሸነፉን ከተገለፀበት ቀን ጀምሮ 5 ቀናት ውስጥ ያሸነፈበትን ገንዘብ ከፍሎ ካለበት ቦታ በራሱ የሰው ሃይል እና ትራንስፖርት አጠቃሎ ማንሳት ግዴታ አለበት፡፡ ይህ ካልሆነ ግን በቅድሚያ ያስያዘው ሲፒኦ ለአሲዮን ማህበሩ ገቢ ይደረጋል፡፡ ተጫራቾች የገዙትን የጨረታ ሰነድ ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ካሉት ተከታታይ ቀናት 7ኛው የስራ ቀን (Working Days) ጠዋት 400 ሰዓት ድረስ በነባር አጠቃላይ ንግድ አክሲዮን ማህበር ህንጻ 2 ፎቅ ላይ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ ጨረታው በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 430 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ማሳሰቢያ - ጨረታው ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ያለው 7ኛው ቀን በዓል ወይም እሁድ ላይ ከዋለ በቀጣዩ የስራ ቀን 400 ሰዓት የጨረታው ሳጥን ተዘግቶ በዚሁ እለት 430 ላይ የሚከፈት ይሆናል፡፡

ሲዮን ማህበሩ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው

ለበለጠ መረጃ:- መረጃ በስልክ ቁጥር 0911-246312 ወይም 0945-986845 መደወል ትችላላችሁ፡፡

 

ነባር አጠቃላይ ንግድ አክሲዮን ማህበር

 

Save Tender