የወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት ለወላይታ ዞን ጤና መምሪያ የጤና ተቋማት ግንባታ ቀሪ ሥራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል፡፡
የግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ወዞፋ/ግ/03/17
የወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት ለወላይታ ዞን ጤና መምሪያ የጤና ተቋማት ግንባታ ቀሪ ሥራ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው ለመሣተፍ የሚችሉ የሥራ ተቋራጮች::
- በኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ተመዝግበው ግብር በመክፈል የ2017 ዓ/ም ፈቃዳቸውን ያሳደሱ፣ የታደሰ ብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ያላቸው፣ ተ.እ.ታ /VAT/ ተመዝጋቢ የሆኑ፣ ቲን /TIN/ መለያ ቁጥር ያላቸው፣ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ ሕጋዊ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው በፌደራል ግዥ እና የመንግሥት ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢነት ምዝገባ /በበይነ መረብ የተመዘገበ እና ማቅረብ የሚችሉ ደረጃ GC-7/BC-7 እና ከዛ በላይ የሆኑ፡፡
- ተጫራቾች ከሚመለከተው አካል የተሰጠ ወቅተዊ ታክስ ክሊራንስ /NVALID TAX CLEARANCE/ ሰርቲፊከት ከመጫረቻ ሠነዳቸው ጋር ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን ሠነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ሕጋዊ ሠነድ በማቅረብ ለሠነዱ የማይመለስ 1000.00 /አንድ ሺህ ብር/ በመክፈል ከወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ግዥ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ከ2ኛ ፎቅ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ጨረታ ሠነድ ውስጥ በተጠቀሰው መሠረት፡-
ሎት 1 ጋልቻ ጤና ጣቢያ የባለሙያዎች ማደሪያ 275,000.00 /ሁለት መቶ ሰባ አምስት ሺህ/ ብር
ሎት 2 ጢዳ ጋርቤ ጤና ጣቢያ የባለሙያዎች ማደሪያ ብር 600,000.00 /ስድስት መቶ ሺህ ብር/፣
ሎት 3. ቦዲቲ የመጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል OPD ስሎክ ብር 525,000.00 /አምስት መቶ ሃያ አምስት ሺህ ብር/
ሎት 4. ሶዶ ጤና ጣቢያ ፋርማሲ ብሎክ 350,000.00 /ሦስት መቶ ሃምሳ ሺህ ብር/
ሎት 5. ጋቼኖ ጤና ጣቢያ ፋርማሲ ብሎክ 175,000.00 /አንድ መቶ ሰባ አምስት ሺህ/
ሎት 6. ዛባ ጤና ጣቢያ የባለሙያዎች ማደሪያ 325,000.00 /ሦስት መቶ ሃያ አምስት ሺህ/ ብር ከጨረታ ሠነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው::
- ተጫራቶች የዋጋ ማቅረቢያውን ሠነድ ኦሪጅናሉን እና ቴክኒካል ሠነድ ኦሪጅናሉን አንድ ላይ በማሸግ እና 2 የኦርጅናሉን ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በማሸግ እና ሁሉንም ፖስታ በአንድ እናት ፖስታ በማድረግ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ሙሉ የፕሮጀክቱን አድራሻና ስም በመጻፍ በዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ መክተት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታው ሣጥን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከ30 ተከታታይ ቀናት ቀጥሎ በሚውለው የሥራ ቀን በ8፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ በ8፡30 ሰዓት በወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ግዥና ንብረት አስተዳደር የጨረታ ክፍል ቢሮ ቁጥር 9 ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በሚያቀርቡት ነጠላ ዋጋ ላይ የማይነበብና ስርዝ ድልዝ ያለው መሆን የለበትም፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ማክፈቻ ዋጋና በሂሣብ ማስተካከያ ዋጋ ልዩነት ከ3% በላይ በሆነ መጠን የሚበልጥ ወይም የሚያንስ መሆን የለበትም፡፡
- ተጫራቾች በዞን እና በሌሎች በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ውስጥ ሲሠሩ ምንም ዓይነት ማስጠንቀቂያ ያልተሰጣቸው መሆን አለባቸው::
- በተጨማሪ እንደገና ተሻሽሎ የወጣው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ግዥ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 70/2017 እና በከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የወጣው የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫ የምዝገባ መመሪያ ቁጥር 648/2013 እና በዚሁ መመሪያ ላይ ማሻሻያ የያዘ ሴርኩላር ተግባራዊ ይሆናል።
- ጽ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 0465512116 ደውለው ማነጋገር ይችላሉ፡፡
ወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
