Tender Detail

Tender Details


የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለብድር ገንዘብ ማካካሻነት በአዋጅ ቁጥር 97/90፣ 216/92 እና 1147/2011 መሰረት በብድር ዕዳ ምክንያት የተረከበውን ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተዘረዘሩትን የመያዣ ንብረቶች በድርድር ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።


የጨረታ ማስታወቂያ

 

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ለብድር ገንዘብ ማካካሻነት በአዋጅ ቁጥር 97/90 216/92 እና 1147/2011 መሰረት በብድር ዕዳ ምክንያት የተረከበውን ከዚህ በታች በሰንጠረዡ የተዘረዘሩትን የመያዣ ንብረቶች በድርድር ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል።

.

 

የተበዳሪው/ የመያዣሰጪው ስም

 

የንብረት አድራሻ

 

የንብረት ዝርዝር

 

የቦታ ስፋት (ሄክታር)

 

የጨረታ መነሻ ዋጋ (በብር)

 

የጨረታ ሁኔታ

 

የጨረታ

ደረጃ

 

ጨረታው የሚካሄድበት ቀንና ሰዓት

 

1

 

ማጃንግ አግሮ ኢንዱስትሪ /የተ/የግል ማህበር

 

ጋምቤላ ///መ፣ ማጃንግ ዞን፣ መንገሺ ወረዳ፣ አሽኔና ባያ ቀበሌ

 

የመስኖ እርሻ እና ግንባታዎች፣ የእርሻ ማሽነሪዎች፣ ተሽከርካሪዎች፣ 145ሄክታር ላይ የተተከለ የሙዝ ቋሚ ተክል ያለው

1000 ሄክታር በሊዝ የተገኘ መሬት

 

375,513,976.00

 

ዝግ

 

የመጀመሪያ

 

ግንቦት 25 ቀን 2017. ከጠዋቱ 400-600 ሰዓት

 

 

 

 ማሳሰቢያ፤

  1. ተጫራቾች የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ በመግዛት ንብረቶቹን የሚገዙበትን ዋጋ፣ ስምና አድራሻቸውን በፎርማቱ ላይ በመጥቀስ በባንኩ ዋና /ቤት ሁለተኛ ታወር ምድር ቤት ለዚሁ ጨረታ በተዘጋጀው ሣጥን ግንቦት 25 ቀን 2017 . ከጠዋቱ 350 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ
  2. ተጫራቾች የጨረታውን መነሻ ዋጋ 10 በመቶ በባንክ ክፍያ ማዘዣ /../ ብቻ በማስያዝ መጫረት ይችላሉ።
  3. አሸናፊ የሆነው ተጫራች ያሸነፈበትን ቀሪ ገንዘብ 15 /በአስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ውስጥ አጠቃሎ ካልከፈለ ያስያዘው ገንዘብ ለባንኩ ገቢ ሆኖ ጨረታው ይሰረዛል።
  4. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሰንጠረዡ በተመለከተው ቀንና ሰዓት በባንኩ ዋናው /ቤት ይካሄዳል።
  5. 15% የተጨማሪ እሴት ታክስና ሌሎች ገዢ እንዲከፍላቸው በሕግ የተወሰኑ ከፍያዎችን፣ የስም ማዛወሪያ ክፍያን ጨምሮ ገዢው ይከፍላል።
  6. አንዳንድ የድርጅቱ ንብረቶች የጉምሩከ ቀረጥና ታከስ ያልተከፈለባቸው ስለሆኑ ገዢው የቀረጥ ነጻ መብት ሊኖረው አሊያም በመንግስት የሚፈለገውን ቀረጥ ለመክፈል ይገደዳል።
  7. የድርጅቱ የስራ እንቅስቃሴ ያልተቋረጠ በመሆኑ አሸናፊው ከግዢው ዋጋ በተጨማሪ ያልተሰበሰበ ወይም በክምችት ላይ ያለ የሙዝ ምርት በርክክብ ወቅት በሚደረስበት የትመና ዋጋ መሰረት በጥሬ ገንዘብ መግዛት ይችላል።
  8. ባንኩ ለሽያጭ የቀረቡትን የመያዣ ንብረቶች የሚሸጠው ሙሉ በሙሉ በጥሬ ገንዘብ ይሆናል።
  9. የጨረታ አሸናፊው የድርጅቱን ቋሚ ሰራተኞች በሙሉ ከመብትና ጥቅማቸው ጋር መረከብ ይጠበቅበታል።
  10.  በጨረታው ላይ መገኘት የሚችሉት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ብቻ ናቸው።
  11.  በጨረታው ዝርዝር እና ተጨማሪ መረጃን ለማግኘት ለማግኘት የኢትዮጵያ ልማት ባንክ ዋና /ቤት ታወር ሁለት ሦስተኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የኦንጎይንግ ኮንሰርን ፕሮጀክትስ እና አኳየርድ አሴትስ ማኔጅመንት ዳይሬክቶሬት በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 011-524-53-73/ 011-524-42-69 ደውሎ ማግኘት ይቻላል፡፡ የመያዣ ንብረቶቹን መጐብኘት የሚፈልግ ከዳይሬክቶሬቱ ጋር አስቀድሞ ቀጠሮ በመያዝ መጐብኘት ይቻላል።
  12.  ባንኩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

 

የኢትዮጵያ ልማት ባንክ

 

Save Tender