የወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት ለወላይታ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የእንስሳት ማቆያ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በ2017 በጀት ዓመት ለወላይታ ዞን ንግድና ገበያ ልማት መምሪያ የእንስሳት ማቆያ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በጨረታው ለመሣተፍ የሚችሉ የሥራ ተቋራጮች
- በኮንስትራክሽን ሚኒስቴር ተመዝግበው ግብር በመክፈል የ2017 ዓ/ም ፈቃዳቸውን ያሳደሱ፣ የታደሰ ብቃት ማረጋገጫ ምስክር ወረቀት ያላቸው፤ ተ.እታ (VAT) ተመዝጋቢ የሆኑ፣ ቲን /TIN/ መለያ ቁጥር ያላቸው፣ ሕጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ ሕጋዊ የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው በፌዴራል ግዥ እና የመንግሥት ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢነት ምዝገባ / በበይነ መረብ የተመዘገቡ እና ማቅረብ የሚችሉ ደረጃ GC-7/BC-7 እና ከዛ በላይ የሆኑ፡-
- ተጫራቾች ከሚመለከተው አካል የተሰጠ ወቅታዊ ታክስ ክሊራንስ /VALID TAX CLEARANCE/ ሰርተፊኬት ከመጫረቻ ሠነዳቸው ጋር ማቅረብ የሚችሉ፣
- ተጫራቾች የተዘጋጀውን ሠነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 30 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ሕጋዊ ሠነድ በማቅረብ ለሠነዱ የማይመለስ 1000.00 /አንድ ሺህ ብር/ በመክፈል ከወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ግዥ ንብረት አስተዳደር ዳይሬክቶሬት በ2ኛ ፎቅ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ጨረታ ሠነድ ውስጥ በተጠቀሰው መሠረት፡- 370,065.00 /ሶስት መቶ ሰባ ሺህ ስልሣ አምስት/ ከጨረታ ሠነድ ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያውን ሠነድ ኦርጅናሉን እና ቴክኒካል ሠነድ ኦርጅናሉን አንድ ላይ በማሸግ እና 2 የኦርጅናሉን ፎቶ ኮፒ ለየብቻው በማሸግ እና ሁሉንም ፖስታ በአንድ እናት ፖስታ በማድረግ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ሙሉ የፕሮጀክቱን አድራሻና ስም በመጻፍ በዚሁ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ መክተት ይኖርባቸዋል።
- የጨረታው ሣጥን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ከ30 ተከታታይ ቀናት ቀጥሎ በሚውለው የሥራ ቀን በ4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዕለቱ በ8፡30 ሰዓት በወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ግዥና ንብረት አስተዳደር የጨረታ ክፍል ቢሮ ቁጥር 9 ይከፈታል።
- ተጫራቾች በሚያቀርቡት ነጠላ ዋጋ ላይ የማይነበብና ስርዝ ድልዝ ያለው መሆን መሆን የለበትም።
- ተጫራቾች እንደገና ተሻሽሎ የወጣው የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል መንግሥት ግዥ አፈጻጸም መመሪያ ቁጥር 70/2017 በከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ሚኒስቴር የወጣው የኮንስትራክሽን ብቃት ማረጋገጫ ምዝገባ መመሪያ ቁጥር 648/2013 እና በዚሁ መመሪያ ላይ ማሻሻያ የያዘ ሰርኩላር ተግባራዊ ይሆናል፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 046551 2116 ደውስው ማነጋገር ይችላሉ፡፡
የወላይታ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
