የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጉምሩክ ኮሚሽን የሰመራ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የተሽከርካሪ ጥገና አገልግሎት (ጋራዥ) ግዥ ብቃትና ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በብሄራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
በድጋሚ የወጣ የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር ፡RE- CC/NCB/SBO/06/2017/25
የተሽከርካሪ ጥገና አገልግሎት (ጋራዥ) ግዥ ጨረታ
- የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጉምሩክ ኮሚሽን የሰመራ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት የተሽከርካሪ ጥገና አገልግሎት (ጋራዥ) ግዥ ብቃትና ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቾች በብሄራዊ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
- ጨረታው የሚከናወነው በኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፑብሊክ መንግሥት በመንግሥት ግዥ አዋጅ በተገለጸው ብሄራዊ ግልጽ ጨረታ ሥነ-ሥርዓት መሠረት ይሆናል፡፡ የጥገና አገልግሎት ግዥ ጨረታ የሚከናወነው ብቁ ከሆነ ተጫራች እና ከአገልግሎቱ ጋር አግባብነት ያላቸው ሆኖ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ስራ ፍቃድ ያለው፣ የዘመኑ ግብር መክፈላቸውን የሚገልጽ ታክስ ክሊራንስ፣ ከመንግስት ግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ ዌብሳይት ላይ የአቅራቢነት ዝርዝር (Supplier List) ፕሪንት አርጎ ማምጣት አለባቸው፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN እና ተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፍኬት ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች በዚህ ጨረታ ለመሳተፍ የማይመለስ ብር 200.00 (ሁለት መቶ ብር) ከፍለው የጨረታ ሰነዱን ከዚህ በታች በተገለጸው አድራሻ በአካል በመገኘት መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን ከዚህ በታች በተራ ቁጥር 7 (ሰባት) በተገለጸው አድራሻ ጨረታው ከወጣበት ግንቦት 02 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ 4፡00 ድረስ ማስገባት ይችላሉ፡፡ ጨረታው ግንቦት 18 ቀን 2017 ዓ.ም ጧት 4:00 ተዘግቶ በዛው ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 4፡30 ላይ ይከፈታል፡፡
- ዘግይተው የቀረቡ የመጫረቻ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም።
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የጨረታ ማስከበሪያ መጠን ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የጨረታው ሰነድ የሚገባበት አድራሻ ጉምሩክ ኮሚሽን የሰመራ ጉ/ቅ/ጽ/ቤት 1ኛ ፎቅ ግዥና ፋይናንስ ቡድን 4ኛ ቢሮ
- ቅ/ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብት አለው።
የጨረታ ሰነድ መሸጫና ጨረታ መክፈቻ ቦታ ሰመራ ጉ/ቅ/ፅ/ቤት ግዥና ፋይናንስ ቡድን አስተባባሪ 1ኛ ፎቅ
ስልክ ቁጥር፡- 03-33-66-88-39/03-33-66-15-67/09-17-35-11-51/09-45-09-17-48
የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ጉምሩክ ኮሚሽን ሰመራ ጉ/ቅ/ፅ/ቤት
