የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለጉራጌ ጤና መምሪያ በጉመር ወረዳ ጀምቦሮ ጤና ጣቢያ ውስጥ በጅምር የቀረውን የፋርማሲ ብሎክ ቀሪ የግንባታ ስራዎች የግንባታ ፍቃድ ያላቸው ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል ።
የጨረታ ማስታወቂያ 5/2017
የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለጉራጌ ጤና መምሪያ በጉመር ወረዳ ጀምቦሮ ጤና ጣቢያ ውስጥ በጅምር የቀረውን የፋርማሲ ብሎክ ቀሪ የግንባታ ስራዎች የግንባታ ፍቃድ ያላቸው ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል ።
ስለዚህ በጨረታው መወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች በማመልከቻ ሲጠየቁ:-
- ደረጃቸው ቢሲ.5/ጂሲ - 5 እና ከዚያ በላይ ፍቃድ ያላቸው፤
- የዘመኑን ንግድ ፈቃድ ያደሱ ሆነው ዋናውንና ኮፒውን ማቅረብ የሚችሉ፤
- የዘመኑን የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እና የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚገልጽ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡
- በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የሚገዙት የጨረታ ሰነድ ጠቅሰው በማመልከቻ ሲጠይቁ ተወካዮች ከሆነ ከድርጅቱ ህጋዊ ውክልና ይዘው መቅረብ አለባቸው፡
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ድረስ የማይመለስ ብር 1000 /አንድ ሺ ብር/ በመክፈል ከጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ቴክኒካልና ፋይናንሻል ዶክመንት ሲያቀርቡ፡-
ሀ/ ለቴክኒካል ዶክመንት አንድ አሪጅናል እና ሁለት ፎቶ ግራፊክ ኮፒዎች እያንዳንዳቸው በሰም በማሸግ ሁሉንም በአንድ ትልቅ እናት ፖስታ በማሸግ የጨረታ ማስከበሪያ 100,00.00 /አንድ መቶ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ፣ ለመቶ ሃያ ቀን የሚቆይ ቢድ ቦንድ ከኦሪጅናል ዶክመንት ጋር በማድረግ /ቴክኒካል በሚል በመለየት/
ለ/ ለፋይናንሺያል ዶክመንት አንድ ኦሪጅናልና ሁለት ፎቶ ግራፊክ ኮፒ በሰም በማሸግ ሁሉንም በአንድ ትልቅ እናት ፖስታ ውስጥ በማሸግ/ ፋይናንሺያል በሚል በመለየት እስከ 21ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት አለባቸው፤
- የጨረታው ማስከበሪያ ሲፒኦ በጉራጌ ዞን ፋ/ኢ/ል መምሪያ ስም መሰራት አለበት፤
- ከተራ ቁጥር 1-7 የተጠቀሱትን መስፈርቶች ሙሉ ለሙሉ ያላሟላ ተጫራች ከውድድር ውጪ ይሆናል፣
- የጨረታው ቴክኒካል ዶክመንት በ21ኛው ቀን ከቀኑ 8፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፣
- የፋይናንሺያል /የፕሮጀክቱ ግንባታ ዋጋ/ ከቴክኒክ ግምገማ ውጤት በኋላ የቴክኒክ ግምገማውን ያለፉት ተጫራቾች ሰነድ ብቻ የጨረታው ኮሚቴው በማስታወቂያ በሚገልፀው ቀን ይከፈታል ፤
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማሳሰቢያ
- በአፈፃፀም ምክንያት ለሶስት ዙር ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው መወዳደር አይችሉም።
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ ወደ ሚቀጥለው የሥራ ቀን ይተላለፋል።
- በጨረታው ሂደት ውስጥ ተሻሽሎ የወጣው የክልሉ የገዢ መመሪያ ተግባራዊ እንደሚደረግ እንገልጻለን/ ዞኑ በሚከታተላቸው ፕሮጀክቶች ከአንድ በላይ ፕሮጀክት ያለው ተቋራጭ መወዳደር አይችሉም፡፡
ለበለጠ መረጃ 0113300112
የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
ወልቂጤ
