የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ) ንብረት የሆኑ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብዓቶች ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ) ንብረት የሆኑ ከባድ የጭነት ተሽከርካሪዎች ባሉበት ሁኔታ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም ተጫራቾች ከዚህ በታች የተመለከቱትን ነጥቦች በማሟላት ቀርበው መወዳደር ይችላሉ፡፡
- ተጫራች በዘርፉ የታደሰ ፈቃድ ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስና የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርበታል፡፡ ለዚህ የተዘጋጀውን ዝርዝር የጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 700.00 (ሰባት መቶ ብር) በመክፈል ከድርጅቱ ንብረት አስተዳደርና ጠቅላላ አገልግሎት ዳይሬክቶሬት በመቅረብ መውሰድ ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች ለሚጫረቱበት ጠቅላላ ዋጋ 20 በመቶ (20%) የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ ከጨረታ ሰነዱ ጋር በማያያዝ ለዚህ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡ የጨረታ ማስከበሪያ ሃያ በመቶ ያላስያዘ ተጫራች ከጨረታው ይሰረዛል፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት በአየር ላይ ቆይቶ በማግስቱ በ16ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት የጨረታው ሳጥን ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በኢኢግልድ ዋና መ/ቤት ስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል። ነገር ግን 16ኛው ቀን በዓል ከሆነ ቀጥሎ ባለው የስራ ቀን ይከፈታል፡፡
- በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች አሸናፊነታቸው በተገለጸላቸው ከ7 የስራ ቀናት በኋላ በ5 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ያሸነፉበትን ዋጋ በሙሉ ገቢ ማድረግ ይኖርባቸዋል፡፡ ሆኖም ሙሉ ክፍያውን በተጠቀሰው ጊዜ ገደብ መክፈል ካልቻሉ ያስያዙት የጨረታ ማስከበሪያ ገንዘብ ለኢኢግልድ ገቢ ሆኖ ኢኢግልድ ሌላ አማራጭ መጠቀም ይችላል፡፡
- የጨረታ ሰነድ የገዙ ተጫራቾች ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ዘወትር በስራ ቀናት ከጠዋቱ 2፡30 እስከ 10፡30 ሰዓት ባለው ጊዜ ውስጥ ፒያሳ ከሊፋ ህንፃ አካባቢ በስተ ሰሜን አቅጣጫ የባቡር ሃዲዱን ተሻግሮ (የቀድሞ ጅንአድ መስሪያ ቤት) አራዳ ክፍለ ከተማ ወረዳ 2 በመሄድ የተሽከርካሪዎችን ዝርዝር መመልከት ይችላሉ፡፡
- ድርጅቱ የተሻለ መንገድ (አማራጭ) ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
አድራሻ አዲስ አበባ በአራዳ ክፍለ ከተማ በወረዳ 02 ፒያሳ ከሊፋ ህንፃ አካባቢ በስተ ሰሜን አቅጣጫ የባቡር ሃዲዱን ተሻግሮ ወደ አራት መንታ በሚወስደው መንገድ ጣልያን ሰፈር (የቀድሞ ጅንአድ መ/ቤት) ፡፡
ተጨማሪ ማብራሪያ ቢያስፈልግ፡- በስልክ ቁጥር 011-8-69-26-84 /011-3-69-19-95 በመደወል ወይም በድረ ገፅ www.mewit.com.et ወይም www.eide.com.et በመጎብኘት ማግኘት ይችላሉ፡፡
የኢትዮጵያ የኢንዱስትሪ ግብአቶች ልማት ድርጅት (ኢኢግልድ)
