የጎንደር መም/ትም/ኮሌጅ የመምህራን መኖሪያ ቤት የሳኒተሪ ጥገና ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጎንደር መም/ትም/ኮሌጅ የመምህራን መኖሪያ ቤት የሳኒተሪ ጥገና ስራ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች መወዳደር የሚችሉ መሆኑን ይጋብዛል።
- በዘመኑ የታደሰ የሚመለከተው ህጋዊ የንግድ ፈቃድ (ውሃ ነክ ስራዎች) ያላቸው፣
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (ቲን ነምበር) ያላቸው።
- የግዥው የብር መጠን 200,000.00 በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ መሆን አለበት።
- ተጫራቾች ከ1 እስከ 3 የተዘረዘሩትን ማስረጃዎች ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ 200 ብር በመክፈል ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21 ተከታታይ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ቢሮ ቁጥር 19 ማግኘት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና የሞሉትን ጠ/ዋጋ 2% በባንክ በተረጋገጠ ሲፒአ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ በአማርኛ የተተረጎመ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማቅረብ አለበት። በጥሬ ገንዘብ የሚያስይዙ ከሆነ በውስጥ ገቢ ደረሰኝ መቁረጥ አለበት፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሰነዱን በአንድ በጥንቃቄ በታሸገ ኢንቨሎፕ ፖስታ በጎንደር መም ኮሌጅ በግ/ፋ/ን/አስ ቢሮ ቁጥር 2 ጋዜጣው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21ኛው መግዛት ይችላሉ። በ22ኛ ቀን 3፡30 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይችላሉ። ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ጎ/መ/ትኮ ቢሮ ቁጥር G 01 በ4፡00 ታሽጎ በ5፡30 ሰዓት ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ቀኑ በዓል ከሆነ የሚቀጥለው ቀን ይከፈታል፡፡
- ኮሌጁ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጨማሪ ማብራሪያ ካስፈለገ ጎ/መ/ት/ ኮሌጅ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0581121634 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ጎንደር መምህራን ትምህርት ኮሌጅ
