አዲስ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ ንግድ ሥራ አ.ማ የጥበቃ እና የጽዳት አገልግሎት አስፈላጊ ግብዓቶችን በሙሉ ተጫራቹ ችሎ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የአገልግሎት ግዥ መፈጸም ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ መለያ ቁጥር 03/2017
አዲስ የካፒታል ዕቃ ፋይናንስ ንግድ ሥራ አ.ማ የጥበቃ እና የጽዳት አገልግሎት አስፈላጊ ግብዓቶችን በሙሉ ተጫራቹ ችሎ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ የአገልግሎት ግዥ መፈጸም ይፈልጋል፡፡
ስለሆነም የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎች በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ።
- ተጫራቾች በዘርፉ ሰፊ ልምድ ያላቸው እና የተሰማሩበትን በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ እስከ ግንቦት 27/2017 ዓ.ም የማይመለስ 300 (ሶስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል የጨረታ ሰነዱን አራት ኪሎ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ህንጻ በሚገኘው አዲስ የካፒታል እቃ ፋይናንስ ንግድ ስራ አ.ማ ዋና መስሪያ ቤት 3ኛ ፎቅ ፋይናንስ አስተዳደር ዳይሬክቶሬት ቢሮ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን 20,000 (ሃያ ሺ ብር) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ኦርጂናል እና ኮፒ በታሽገ ኤንቨሎፕ በማድረግ እስከ ግንቦት 27/2017 ዓ.ም 4፡00 ድረስ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው በ27/9/2017 ዓ.ም በ 4፡00 ተዘግቶ በእለቱ በ4፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ወረድ ብሎ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ህንጻ 3ኛ ፎቅ በሚገኘው የአዲስ ካፒታል እቃ ፋይናንስ ንግድ ስራ አ.ማ ዋናው መ/ቤት ይከፈታል፡፡
- ኩባንያው ጨረታውን በከፊል ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ፡
አራት ኪሎ ቱሪስት ሆቴል ወረድ ብሎ የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት ህንጻ 3ኛ ፎቅ
ለበለጠ መረጃ ስልክ ቁጥር 011-1-26-38-88 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
አዲስ የካፒታል እቃ ፋይናንስ ንግድ ስራ አ.ማ.
