ኩባንያችን ጢስ እሳት ውሃ ስራዎች የአንቲ ቫይረስ፤ የኔትዎርክ ደህንነት መቆጣጠሪያ (Firewall)፣ ዲጅታል ሳይንኤጅ /Floor standing digital signage/፣ የተለያዩ መለዋወጫዎች፤ የመበየጃ ጄኔሬተሮች እና የቧንቧ መገጣጠሚያ ፊቲንጎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
ኩባንያችን ጢስ እሳት ውሃ ስራዎች የአንቲ ቫይረስ፤ የኔትዎርክ ደህንነት መቆጣጠሪያ (Firewall)፣ ዲጅታል ሳይንኤጅ /Floor standing digital signage/፣ የተለያዩ መለዋወጫዎች፤ የመበየጃ ጄኔሬተሮች እና የቧንቧ መገጣጠሚያ ፊቲንጎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
|
ሎት |
የእቃው አይነት |
የጨረታ ማስከበሪያ |
የማቅረቢያ ቀን |
|
ሎት 1 |
አንቲቫይረስ |
50,000.00 |
በ15 ቀን |
|
ሎት 2 |
የኔትወርክ ደህንነት መቆጣጠሪያ (Firewall) |
50,000.00 |
በ30 ቀን |
|
ሎት 3 |
ዲጅታል ሳይንኤጅ /Floor standing digital signage/ |
30,000.00 |
በ30 ቀን |
|
ሎት 4 |
የተለያዩ መለዋወጫዎች |
100,000.00 |
ከ45-60 ቀን |
|
ሎት 5 |
የመበየጃ ጄኔሬተሮች Welding Generators/ |
50,000.00 |
ከስቶክ |
|
ሎት 6 |
ቧንቧና የቧንቧ መገጣጠሚያ ፊቲንጎች |
100,000.00 |
ከ45-60 ቀን |
ስለዚህ ማንኛውም በዘርፉ የተሰማራና በጨረታዉ መሳተፍ የሚፈልግ አቅራቢ ድርጅት ዝርዝር የጨረታ ሰነዱን በድርጅታችን ዌብ ሳይት www.tisisat.com ማግኘት ይችላል። የተጫራቾች መመሪያ፤
- ተጫራቾች የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የንግድ ምዝገባ የምሰክር ወረቀት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የTIN ሰርተፍኬት፣ በዘርፉ ለመሰማራት የተሰጣቸውን ፈቃድ እና ተያያዥነት ያላቸውን ማስረጃዎች ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ጨረታው ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ21ኛው ቀን ከቀኑ 9፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ቀን ከቀኑ 9፡30 ሰዓት ባህርዳር ከተማ አባይ ማዶ ቴዲ የአሽከርካሪዎች ማሰልጠኛ ጎን በሚገኘው ዋናው መ/ቤት ተጫራቾች እና ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ቀን የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት ተዘግቶ ይከፈታል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በድርጅታችን ዌብ ሳይት www.tisisat.com ማግኘት ይችላሉ።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ በሰንጠረዥ የተመለከተውን ገንዘብ በCPO ወይም ያለቅድመ ሁኔታ እንደተጠየቀ ለገዥ የሚከፈል (unconditional Bank Guarantee) ማስያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ የሚያወጡት ወጪ በተጫራቹ የሚሸፈን ይሆናል።
- ተጫራቾች የዋጋ ማቅረቢያቸውን እና ቴክኒካል ሰነዳቸውን ለየብቻ በተለያየ ፖስታ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ተጫራች ድርጅቶች ለሚያቀርቡት ዋጋ ለእያንዳንዱን እቃ ነጠላ ዋጋ እና ጠቅላላ ዋጋ በትክክል ሞልተው በግልፅ ማስቀመጥ አለባቸው።
- ይህ ጨረታ በኩባንያችን የግዥ መመሪያ ነሃሴ /2013/ መሰረት ተፈፃሚ ይሆናል።
- ኩባንያው በጨረታ ሰነዱ ላይ ከተገለፀው መጠን 25% ቢጨምር ወይም ቢቀንስ የጨረታ አሸናፊው ውል የመያዝ ግዴታ ይኖርበታል።
- የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ በጽሁፍ ከተገለጸበት ቀን ጀምሮ በ05 ቀናት ውስጥ የጠቅላላ ዋጋውን 10% የውል ማስከበሪያ ያለቅድመ ሁኔታ ለገዥ የሚከፈል (unconditional Bank Guarantee) በማሰራት ውል የመያዝ ግዴታ ይኖርበታል።
- የማቅረቢያ ጊዜ ከላይ በሰንጠረዡ ላይ በተገለፀው መሠረት መሆን አለበት። የአቅራቢዎች ዋጋ ቢያንስ ለ90 ቀናት ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ፀንቶ መቆየት አለበት።
- ኩባንያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ በዚህ ጨረታ አይገደድም ወይም ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ዕቃው ወይም አገልግሎቱ የሚቀርብበት ቦታ ባህር ዳር ከተማ የኩባንያው ጽ/ቤት መሆን አለበት።
- ማሳሰቢያ፡- እንደ ኩባንያችን ፍላጎት ውድድሩ በሎት ወይም በእያንዳንዱ እቃ ነጠላ ዋጋ መሠረት ሊሆን ይችላል።
ለበለጠ መረጃ፡- በስልክ ቁጥራችን 058-220-4826/058-320-2548/ በፋክስ ቁጥራችን 058 220 4830 መጠየቅ ይችላሉ።
