የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች የተጠቀሰውን አገልግሎት /እቃ/ ግዥ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች የተጠቀሰውን አገልግሎት /እቃ/ ግዥ በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ሎት:- 1 ላፕቶፕ ኮምፒውተር
ሎት፡- 2 ፕሪንተር
በዚሁ መሠረት ከላይ ለተገለፀው ግዥ ተጫራቾች ለሚወዳደሩበት የግዥ ዓይነት በዘርፉ ታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ (Value added tax) ተመዝጋቢ መሆናቸውን፣
ግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN)፣ የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀቶች፣ በአቅራቢነት ድህረ- ገፅ (WebSite) ዝርዝር ላይ የተመዘገቡበትን የሚያሳይ ምስክር ወረቀት እና በጨረታ መሳተፍ ሚያስችላቸው ከገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የሚሰጥ የታክስ ክሊራንስ ማስረጃ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተወዳዳሪዎች በጨረታ እንዲሣተፉ ይጋብዛል፡፡
- ተጫራቾች እያንዳንዱን የሚወዳደሩበትን ጨረታ ሠነድ ላይ የተገጸውን የዕቃውን /የአገልግሎት/ ዝርዝር መግለጫ መሠረት በማድረግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፣
- ተጫራቾች የጨረታ ሠነዱን በዚህ ማስታወቂያ በስተመጨረሻ በተገለጸው አድራሻ በቢሮ ቁጥር ብሎክ 2 በግንባር በመቅረብ ለእያንዳንዱ ሎት የማይመለስ ብር 300.00 / ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፤
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታውን ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 15 ቀናት በሎጀስቲክስና ፕሮኪዩርመንት ዳይሬክቶሬት ብሎክ ቁጥር 7 በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይኖርባቸዋል፣
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ማለትም በ16ኛው ቀን በአል ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን 4፡00 ላይ ታሽጎ 4፡30 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልጽ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተረጋገጠ ሲ.ፒ.ኦ (C.P.O) 100,000.00 /አንድ መቶ ሺህ / ብር ብቻ በኮርፖሬሽኑ ስም ዋስትና ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ቴክኒካልና ፋይናንሻል ኦሪጅናልና ኮፒዎችን ለየብቻው በትልቅ ፖስታ በማሸግና የድርጅቱን ማህተም በማድረግ ማስገባት አለባቸው፣
- በጨረታው አሸናፊ የሆኑ ተጫራቾች ያሸነፉባቸውን ዕቃዎች ጠቅላላ ዋጋ 10% የውል ማስከበሪያ በባንክ የተረጋገጠ C.P.O በማስያዝ ውል የመዋዋል ግዴታ አለባቸው፣
- ኮርፖሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ሆነ በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለተጨማሪ መረጃ ኮርፖሬሽኑ የሚገኘው 22 ማዞሪያ አውራሪስ ሆቴል አጠገብ ብሎክ ቁጥር 7 በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 0913705481 በመደወል መረጃ ማግኘት ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ማዕድን ኮርፖሬሽን
