የአማን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባለቤትነት በ2017 በጀት አመት ሊያስራ ባቀደው ተጀምሮ ሳይጠናቀቅ የቆየው የመማሪያ ክፍል የማስጨረስ ስራ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአማን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ባለቤትነት በ2017 በጀት አመት ሊያስራ ባቀደው ተጀምሮ ሳይጠናቀቅ የቆየው የመማሪያ ክፍል የማስጨረስ ስራ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾችን በጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ በዚህም መሰረት፡-
- ደረጃ 6 GC/BC እና ከዛ በላይ የሆነ
- ተጫራቾች ሰነድ ለመግዛት በሚገዙበት ጊዜ ለበጀት አመቱ የሚያገለግል የብቃት ማረጋገጫ፣ የንግድ ፍቃድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት፣ የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፍኬት ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር የምስክር ወረቀት በማቅረብ በተቋሙ ግ/ፋ/ን/ቢሮ ቁጥር 9 የጨረታውን ሰነድ የማይመለስ 1000 ብር በመክፈል መግዛት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ በተገቢው ሁኔታ ማቅረብ የሚችል አቅራቢነት የምስክር ወረቀት እና ከግብር ነጻ መሆኑን የሚገልጽ ማስረጃ ማቅረብ የሚችል።
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 80,000 /ሰማንያ ሺህ ብር/ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማስያዝ አለበት፡፡
- ተጫራቾች የገዙትን ሰነድ /ፋይናንሻልና ቴክኒካል/ ከላይ የተዘረዘሩትን አስፈላጊ የሆኑትን መረጃዎች በእያንዳንዳቸው አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ በሰም በታሸገ ፖስታ ማቅረብ የፋይናሻል እና ቴክኒካል ዶክመንቱን በጥቅሉ በአንድ ፖስታ መታሸግ አለባቸው።
- እያንዳንዱ ፖስታ በሰም ታሽጎ ማህተም መመታቱንና ሙሉ አድራሻ በመጻፍ በመፈረም እና ኦርጅናልና ኮፒ በግልጽ የሚታይ ቦታ ላይ መጻፍ አለበት፡፡ እንዲሁም የድርጅቱ ማህተም መኖር አለበት፡፡
- ተጫራቾች በሁሉም ዋጋ ማቅረቢያ እና ቴክኒካል ሰነዶች ላይ የተጫራቾች ህጋዊ ወኪል ፊርማ እንዲሁም የድርጅቱ ማህተም መኖር አለበት፡፡
- እያንዳንዱ ፖስታ የሚወዳደሩበት የስራ ቦታ፣ የተቋራጩ አድራሻ፣ የድርጀቱ ወይም የተወካዩ ስልክ ቁጥር በግልጽ መጻፍ አለበት።
- ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 21 ተከታታይ ቀናት ማንኛውም ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ቴክኒካል ዶክመንት አንድ ኦርጅናልና ሁለት ኮፒ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው የሚታሸገው የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21 ቀን በአማን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር 9 ከጠዋቱ 4:00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ተወካዮቻቸው በተገኙበት ይታሸጋል፡፡
- ጨረታው የሚከፈተው የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን በ21ኛው ቀን በአማን ፖሊ ቴክኒከ ኮሌጅ ቢሮ ቁጥር 9 ከሰዓት በኋላ ከቀኑ 8:00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ተወካዮቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ኮሌጁ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ በህግ የተጠበቀ ነው።
የአማን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ
