የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት የአፈጻጸም ክርክር በተመለከተ በፍርድ ባለእዳው ሥም ተመዝግቦ የሚገኝ የሰሌዳ ቁጥር ኢት-3-40011 መኪና በጨረታ እንዲሸጥ ፍርድቤቱ አዟል። ስለሆነም ፍላጎት ያላችሁ ሰዎች መኪናው በሚገኝበት ቦታ በአዳማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመገኘት በዚህ ጨረታ ላይ እንድትሳተፉ ይጋብዛል።
የጨረታ ማስታወቂያ
በፍ/ርድ ባለመብት አቶ ሁሴን ኡመር እና በፍ/ርድ ባለእዳ አቶ መሐመድ ሐሰን ኡመር መካከል ስላለው የአፈጻጸም ክርክር በተመለከተ በፍርድ ባለእዳው ሥም ተመዝግቦ የሚገኝ የሰሌዳ ቁጥር ኢት-3-40011 መኪና በጨረታ መነሻ ብር 2,331,501.74 /ሁለት ሚሊዮን ሶስት መቶ ሰላሣ አንድ ሺህ አምስት መቶ አንድ ብር ከ74/100ሣ/ በጨረታ እንዲሸጥ ፍርድ ቤቱ አዟል። በዚህ መሠረት በ21/10/2017 ከጠዋቱ 3፡30 እስከ ቀኑ 6፡00 ድረስ የሚሸጥ ስለሆነ ለመግዛት ፍላጎት ያላቸው ሰዎች መኪናው በሚገኝበት ቦታ በአዳማ ከተማ ፖሊስ መምሪያ በመገኘት እንድትገዙ እያሳሰብን የጨረታ መነሻውን ግምት 25 ፐርሰንት በስንቄ ባንክ በሲፒኦ የሂሣብ ቁጥር 1079213271818 በሆነው ላይ በማስያዝ እንዲወዳደሩ እና ውጤቱን በ24/10/2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 5፡00 ሰዓት ላይ እንዲቀርብ ሲል የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት አዟል።
የአዳማ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት
