ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የተገለፁትን ተሽከርካሪ ግዥ ለመፈጸም በዘርፉ የተሰማሩ አቅራቢ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የተሽከርካሪ ግዥ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር አመሥድ 21/2017
ኮርፖሬሽናችን ከዚህ በታች በሰንጠረዥ የተገለፁትን ተሽከርካሪ ግዥ ለመፈጸም በዘርፉ የተሰማሩ አቅራቢ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
|
ተ.ቁ |
የተሽከርካሪው አይነት |
ብዛት |
ተሽከርካሪው የሚቀርብበት ቦታ |
ምርመራ |
|
1 |
Low Bed Truck |
01 |
አዲስ አበባ ማስተባበሪያ ቢሮ |
|
ስለዚህ ከዚህ በታች የተገለፁትን የጨረታ መወዳደሪያ መስፈርቶችን የሚያሟላ ማንኛውም አቅራቢ ድርጅት በጨረታው መወዳደር ይችላል።
- በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የተ.እ.ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑና የግብር ከፋይነት ምዝገባ ሰርተፊኬት ቁጥር እና ግብር ስለመክፈላቸው የግብር ክሊራንስ ሰርተፍኬት ያላቸው።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚውል ሲፒኦ ወይም ያለቅድመ ሁኔታ እንደተጠየቀ የሚከፈል ባንክ ጋራንቲ የተ.እ.ታክስን ጨምሮ ለሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ 500,000.00 (አምስት መቶ ሺህ ብር) ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ ለ90 ቀን የሚቆይ ማስያዝ አለባቸው።
- መ/ቤቱ አሸናፊውን ተጫራች ድርጅት በሚመርጥበት ጊዜ የተሽከርካሪዎችን መጠን እንደአስፈላጊነቱ እስከ 50% ሊጨምር ይችላል።
- ተጫራቾች ከላይ በሰንጠረዥ ለተገለፀው ተሽከርካሪ አስፈላጊ መረጃዎችን መጥቀስ እና ማያያዝ አለባቸው።
- ተጫራቾች የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ማለትም ዋጋ መሙያ ሰነዳቸውን ኮፒ እና ኦርጅናል ለየብቻ እንዲሁም የቴክኒካል የመጫረቻ ሰነዳቸውን ማለትም የንግድ ስራ ፍቃድ፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ሰርተፍኬት፤ የግብር ከፋይ ሰርተፍኬት እና ሌሎች የተሽከርካሪዎችን የቴክኒካል ሰነዶችን እና ሌሎች አስፈላጊ ዶክመንቶችን ኮፒ እና ኦርጅናል ለየብቻ በተጨማሪም የጨረታ ማስከበሪያቸውን ለብቻ በፖስታ አድርገው በአንድ በታሸገ ኢንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 20 ተከታታይ ቀናት ውስጥ የመወዳደሪያ ሰነዳቸውን ባሕርዳር ከተማ ከሚገኘው ዋና መ/ቤታችን ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን አማራ ፓይፕ ፋብሪካ ፊት ለፊት የመሳሪያ እና መለዋወጫ ቡድን ቢሮ በመቅረብ ለጨረታው በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ጨረታው በ20ኛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ተዘግቶ (ታሽጎ) በዚሁ ቀን 4፡30 ይከፈታል። ይሁን እንጂ 20ኛው የመክፈቻ ቀን ከኮርፖሬሽናችን የስራ ሰዓት ውጭ ከሆነ እና የመንግስት ካላንደር የሚዘጋው ከሆነ በቀጣዩ የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት የሚከፈት ይሆናል።
- በጨረታው በተገለፀው ተሽከርካሪ ዝርዝር የጨረታ ሰነድ ብር 300.00 (ሶስት መቶ ብር ብቻ) በመክፈል ከኮርፖሬሽናችን ገንዘብ ያዥ ቢሮ ቁጥር 23 ቀርበው መግዛት ይችላሉ።
- ኮርፖሬሽናችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ኮርፖሬሽናችን የቴክኒካል ገጽ ሰነድ ከፋይናንሻል መሙያ ሰነድ ጋር ይያያዛል።
- ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር 058-320-35-76 መደወል ይችላሉ።
ኅብር ኮንስትራክሽን ኮርፖሬሽን
