በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ለዲስትሪክታችን ሰራተኞች እና በዲስትሪክታችን እየተሰራ ለሚገኘው ለድሬዳዋ መልካ ጀብዱ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ለሰርቪስ አገልግሎት የሚውል በቁጥር 1 (አንድ) የህዝብ ማመላለሻ አውቶቢስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል፡፡
የህዝብ ማመላለሻ አውቶቢስ ኪራይ ጨረታ ማስታወቂያ
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ለዲስትሪክታችን ሰራተኞች እና በዲስትሪክታችን እየተሰራ ለሚገኘው ለድሬዳዋ መልካ ጀብዱ የመንገድ ስራ ፕሮጀክት ለሰርቪስ አገልግሎት የሚውል በቁጥር 1 (አንድ) የህዝብ ማመላለሻ አውቶቢስ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መከራየት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም አከራዮች የሚያቀርቡት የህዝብ ማመላለሻ አውቶብስ የስሪት ጊዜው እ.ኤ.አ ከ2012 ጀምሮና የመያዝ አቅሙ 60 (ስልሳ) የመቀመጫ ወንበር ያሉት ሆኖ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ከሆነ በግልጽ ጨረታው እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡-
- የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለውና የዘመኑን ግብር የከፈለ፣
- የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ ሰርተፊኬት ያለው/ያላት፣
- የባለቤትነት ሊብሬ የሚያቀርብ፣
- የ3ኛ ወገን መድን ሽፋን የተገባለት፣
- ነዳጅ እንዲሁም የጥገና፣ የሾፌር ደሞዝና አበል በአከራይ ይሸፈናል፡፡
- ለህዝብ ማመላለሻ አውቶቢስ በቀን የሚከራይበትን ዋጋ ድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት ከሚገኘው ቢሮአችን በአካል በመቅረብ የጨረታ ሰነድ በመውሰድ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ማቅረብ አለበት፡፡
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 (አስራ አምስት) የስራ ቀናት ክፍት ሆኖ ቆይቶ በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡30 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 5፡00 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ድሬዳዋ በሚገኘው የድርጅቱ ዋና ቢሮ የስብሰባ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- የጨረታው መዝጊያና መክፈቻ ዕለት የስራ ቀን ካልሆነ ጨረታው በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
- አሸናፊ ተጫራቾች የቴክኒክ ምርመራውን ካለፈ ውል በመፈፀም ወዲያውኑ ወደ ሥራ መሰማራት አለባቸው፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብት አለው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ
በስልክ ቁጥር +0251 11 13 13/092 906 32 49/09-67-47-44-90/09-19-00-80-17 በመደወል መጠየቅ ይቻላል።
በኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር የድሬዳዋ መንገድ ጥገና ዲስትሪክት
