የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነገሮች ለመግዛት በግልጽ ጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የአዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ በ2018 ዓ.ም የበጀት ዓመት፡-
- የተለያዩ ህትመቶች ለአንደኛ ጊዜ ለማሳተም
- የፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ ሥራ ለአንደኛ ጊዜ ለማሰራት
- የጽዳት ስራ ለሁለተኛ ጊዜ በ “out source” ለማሰራት
- ለኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች ለአንደኛ ጊዜ ለመግዛት በግልጽ ጨረታ ማወዳደር ይፈልጋል፡፡
- በመሆኑም ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ነጋዴዎች መወዳደር ትችላላችሁ፡፡
- ለ2017 ዓ.ም የታደሰ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ በዘርፉ ያላችሁ፡፡
- ተጫራቾች የተጨማሪ እሴት ታክስ (VAT) ተመዝጋቢ ለመሆናቸው መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- በገንዘብና ኢኮኖሚ ልማት ፅ/ቤት በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ መመዝገባቸውን የሚያረጋግጥ መረጃ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች የሚያቀርቡትን የጨረታ ሰነድ ኮፒና አሪጅናል ለየብቻ በተለያየ ፖስታ ማሸግ አለባቸው።
- ስርዝ ድልዝ ያለው፣ የማይታይ የጨረታ ሰነድ ወይም የዋጋ ዝርዝር ተቀባይት የለውም፡፡
- ጨረታውን ካሸነፉ በኋላ የውል ማስከበሪያ ያሸነፉበትን ዋጋ 10% ማስያዝ የሚችሉ፡፡
- ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከኮሌጁ ግዥና ፋይናንስ የስራ ሂደት ከፍል ዘወትር በስራ ሰዓት የማይመለስ ለእያንዳንዱ ጨረታ 200 (ሁለት መቶ) ብር በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ አለባቸው።
- ለጽዳት ስራ ከአዳማ ከተማ የምግብ ዋስትና እና የስራ ፈጠራ ክህሎት ከጥቃቅንና አነስተኛ ኢንተርፕራይዝ የድጋፍ ደብዳቤ ማምጣት የሚችሉ እና በጽዳት ስራ ላይ በIMX የተደራጁ መሆን አለባቸው።
- የተለያዩ ህትመቶች ጨረታው የሚከፈተው በ26/10/2017 ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- የፈሳሽ ቆሻሻ ማስወገጃ/ ሥራ ጨረታው የሚከፈተው በ26/10/2017 ከቀኑ 9፡30 ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- የጽዳት ስራ “out source" ጨረታው የሚከፈተው በ27/10/2017 ከቀኑ 8፡30 ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- የኤሌክትሮኒከስ ዕቃዎች ጨረታው የሚከፈተው በ27/10/2017 ከቀኑ 9፡30 ተጫራቾች/ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች የሚሞሉትን ዋጋ በመስሪያ ቤቱ ሰነድ ብቻ ላይ መሆን አለበት፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ ለእያንዳንዱ 10,000 (አስር ሺህ) ብር በ"CBE, CBO እና Singe ባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ብቻ ማስያዝ የሚችል መሆን አለበት፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0228123956 ደውለው መረዳት ይችላሉ፡፡
አዳማ ሆስፒታል ሜዲካል ኮሌጅ
