የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ሣምንታዊ የግምጃ ቤት ሰነድ በጨረታ ቁጥር 980 ለሽያጭ አቅርቧል።
የኢትዮጵያ መንግሥት የግምጃ ቤት
ሰነድ የጨረታ ማስታወቂያ
- ሣምንታዊ የግምጃ ቤት ሰነድ ጨረታ ቁጥር 980
- ለሽያጭ የቀረበው ሰነድ ጠቅላላ ዋጋ ብር 20,873,710,000
- ሰነዶቹ ለገበያ የሚቀርቡበት ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም
- የሰነዶቹ ዓይነትና ለጨረታ የሚቀርበው የገንዘብ ልከ፣
|
የሰነዱ ዓይነት |
የገንዘብ ልክ |
የሚከፈልበት ጊዜ |
|
የ 28 ቀን |
1,461,160,000 |
ሐምሌ 16 ቀን 2017 ዓ.ም |
|
የ 91 ቀን |
2,713,580,000 |
መስከረም 14 ቀን 2018 ዓ.ም |
|
የ 182 ቀን |
5,218,430,000 |
ታኅሣሥ 15 ቀን 2018 ዓ.ም |
|
የ 364 ቀን |
11,480,540,000 |
ሰኔ 17 ቀን 2018 ዓ.ም |
- የእያንዳንዱ የግምጃ ቤት ሰነድ መነሻ መደብ ብር 5,000 ሆኖ ከዚህ በላይ ለሚፈልጉ የመነሻ ብዜት ይሆናል፡፡
- ማንኛውም ተጫራች ለሁሉም ወይም ለየትኛውም የሠነድ ዓይነት መጫረት ይችላል፡፡
- የጨረታ ማቅረቢያ ቅጽ ከክፍያና የሂሣብ ማወራረጃ ሥርዓት ዳይሬክቶሬት ማግኘት ይቻላል፡፡
- የጨረታ ማመልከቻ ማቅረቢያ የመጨረሻ ቀን ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም እስከ 5፡30 ሰዓት
- የጨረታ ውጤት ሰኔ 18 ቀን 2017 ዓ.ም ይገለጻል፡፡
- ከግምጃ ቤት ሰነድ ጋር በተያያዘ የሚገኝ ገቢ ወይም ትርፍ ከማናቸውም ዓይነት ታክስ ነጻ ነው፡፡
- ተጨማሪ መረጃ ከክፍያና የሂሣብ ማወራረጃ ሥርዓት ዳይሬክቶሬት ወይም ከባንኩ ድረ ገጽ www.nbe.gov.et ማግኘት ይቻላል፡፡
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ
