የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ከዚህ በታች የቀረቡትን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ማለትም የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እና የኔትወርክ ዕቃዎች፣ የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች የህትመት ስራዎች ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር ከዚህ በታች የቀረቡትን ዕቃዎች እና አገልግሎቶች ማለትም የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እና የኔትወርክ ዕቃዎች፣ የጽህፈት መሣሪያዎች፣ የጽዳት ዕቃዎች የህትመት ስራዎች ግዥ በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
በዚሁ መሰረት ከዚህ በታች የተገለፀውን መስፈርት የሚያሟሉ ተጫራቾች በጨረታው እንዲወዳዳሩ ተጋብዘዋል።
- በዘርፉ ህጋዊ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ እና በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ማስረጃ (ክሊራንስ) ማቅረብ አለባቸው።
- የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ የሆኑ እና የንግድ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ማንኛውም ተጫራች ጨረታው ከተከፈተ በኋላ በጨረታው ሰነድ ላይ የተገለጸውን ማናቸውንም ሁኔታዎች መለወጥ ወይም ማሻሻል ወይም ከጨረታው መውጣት አይችልም።
- የሚገዙ ዕቃዎች በተሰጠው ስፔስፊኬሽን እና በናሙና መሰረት አሟልቶ ላልቀረበ ማንኛውም ሁኔታዎች ስህተት ቢፈጸም ኃላፊነቱ የተጫራቾች /የአቅራቢው/ ድርጅት ይሆናል።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ በባንክ በተመሰከረለት CPO /ሲፒኦ/ ወይም የባንክ ዋስትና በአስተዳደሩ ስም ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 200 /ሁለት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ማስታወቂያው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ ቀናት የሚቆይ ሲሆን ጨረታው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከጠዋቱ 2፡00 እስከ ቀኑ 11፡00 ድረስ መግዛት ይችላሉ። ጨረታው በ16ኛው የስራ ቀን በ4፡00 ታሽጎ በዚያው ዕለት በ4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል። ይሁን እንጂ 16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
- ተጫራቾች ለሚጫረቱባቸው የጽ/መሳሪያዎች ፣ የጽዳት ዕቃዎች ናሙና /ሳምፕል ጨረታው ከመከፈቱ በፊት በአስተዳደሩ ንብረት ክፍል ማስገባት እና ስለማስገባታቸው ለግዥ የሥራ ክፍል ገቢ የተደረገበትን ማሰረጃ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ዕቃዎች ሙሉ በሙሉ ኦሪጅናል መሆን አለባቸው።
- ተጫራቾች ለወረቀት የህትመት ሥራዎች አስተዳደሩ የሚያቀርበውን ናሙና መውሰድ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነድ ዋናውንና ኮፒውን የቴክኒክና ፋይናንስ ሰነዶችን በተናጠል በታሸገ ኢንቨሎፕ የድርጅቱን ማህተም በማድረግ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ለጨረታው የሚቀርበው ሰነድ ስርዝ ድልዝ የሌለበት ሆኖ የሚቀርበው ዋጋ በግልጽ መጻፍ ይኖርበታል። ስርዝ ድልዝ ወይም አሻሚ የሆነ ዋጋ ከቀረበ ተጫራቹ ከውድድር ውጪ ይደረጋል።እንዲሁም በአስተዳደሩ ተዘጋጅቶ በጨረታ ሰነድ ላይ ብቻ ዋጋ መሞላት አለበት።
- አሸናፊ ድርጅት ባሸነፈባቸው ዕቃዎች ከጠቅላላ ዋጋ 10% ለድርጅቱ ውል ማስከበሪያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታውን አሸንፎ በወቅቱ ውል ለማሰር ፈቃደኛ ያልሆነ ተጫራች በጨረታ ያስያዘው የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ /ሲፒኦ/ ለአስተዳደሩ ገቢ ይደረጋል። በቀጣይም አስፈላጊው አሰተዳደራዊ እርምጃ ይወሰዳል።
- አስተዳደሩ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
|
ተ.ቁ |
የግዥው አይነት |
የጨረታ ቁጥር |
የጨረታ ማስከበሪያ የገንዘብ መጠን |
|
ሎት 1 |
የተለያዩ የኤሌክትሮኒክስ እና የኔትወርክ ዕቃዎች |
የግድሠማዋኦ ብግጨ/01/01/2018 |
200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ በር/ |
|
ሎት 2 |
የጽህፈት መሣሪያዎች |
የግድሠማዋኦ ብግጨ/01/02/2018 |
200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ በር/ |
|
ሎት 3 |
የጽዳት ዕቃዎች |
የግድሠማዋኦ ብግጨ/01/03/2018 |
150,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ በር/ |
|
ሎት 4 |
የህትመት ስራዎች |
የግድሠማዋኦ ብግጨ/01/04/2018 |
100,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ በር/ |
አድራሻችን፡- አዲስ አበባ መገናኛ ቦሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ፊት ለፊት ወይም መገናኛ ሕዳሴ ህንጻ ወረድ ብሎ
የአስተዳደሩ ዋና መ/ቤት የግዥ ዳይሬክቶሬት 1ኛ ፎቅ
ለበለጠ ማብራሪያ ስልከ ቁጥር +251-111-56-88-90
የግል ድርጅት ሠራተኞች ማህበራዊ ዋስትና አስተዳደር
