የፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ለ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ከዚህ በታች በምድብ የተገለጹ ዝርዝሮች በዘርፉ ከተሰማሩ ተጫራቾች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
የጨረታ ጥሪ ማስታወቂያ
ጨረታ ቁጥር ግ001/2018 በጀት ዓመት
የፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ ለ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ከዚህ በታች በምድብ የተገለጹ ዝርዝሮች በዘርፉ ከተሰማሩ ተጫራቾች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
|
ምድብ ቁጥር |
አገልግሎት/ የዕቃው ዓይነት |
የጨረታ ሰነዱ ዋጋ |
የጨረታ ማስከበሪያ |
|
ምድብ 1 |
ገረጋንቲ ድንጋይ |
400.00 |
150,000.00 (አንድ መቶ ሀምሳ ሺህ) በሲፒኦ |
|
ምድብ 2 |
ቦልድ ድንጋይ |
400.00 |
130,000.00 (አንድ መቶ ሰላሳ ሺህ) በሲፒኦ |
|
ምድብ 3 |
የደረቅ ቆሻሻ መጣያ የሚያገለግል ደስትቢን |
400.00 |
140,000.00 (አንድ መቶ አርባ ሺህ) በሲፒኦ |
|
ምድብ 4 |
በፖለት ደረጃ የሚበሰብስ እና የማይበሰብስ የሚለይበት፡- የኤጀንሲው ሎጎ የታተመበት ከረጢት ማዳበሪያ ግዥ |
400.00 |
40,000.00 (አርባ ሺህ) በሲፒኦ |
|
ምድብ 5 |
የትራፊክ አደጋ ምልክት (Traffic Protective Cones) |
400.00 |
30,000.00 (ሰላሳ ሺህ) በሲፒኦ |
|
ምድብ 6 |
የተለያዩ የኩነት አገልግሎት ግዥ (ኢቨንት ኦርጋናይዜሽን) |
400.00 |
30,000.00 (ሰላሳ ሺህ) በሲፒኦ |
|
ምድብ 7 |
የተለያዩ ህትመቶች ግዥ |
400.00 |
45,000.00 (አርባ አምስት ሺህ) |
ስለሆነም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች :-
- ተጫራቾች አግባብነት ያለው ለዘመኑ የታደሰ ንግድ ሥራ ፍቃድ፣ የንግድ ምስክር ወረቀት፣ ተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት እና በጨረታ መወዳደር የሚያስችል የዘመኑ ግብር የከፈሉበት ታክስ ክሊራንስ እንዲሁም በመንግሥት ግዥና ንብረት አስተዳደር አዋጅ ድረ-ገጽ (WWW.PPA.gov.et) የአቅራቢዎች ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆን ይኖርባቸዋል፤ በተጨማሪም ቦለድ ድንጋይ እና ገረጋንቲ ግዥ የምትሳተፉ ተጫራቾች በሕግ አግባብነት ካለው አካል የተሰጠ ለሰብ ቤዝ (የተቆፋሪ ማዕድን) ለማውጣትና ለገበያ ለማቅረብ የሚያስችል የማምረቻ ቦታ ኳሪ እና የባለቤትነት ፍቃድ፤ ወይም በሰነዶች ማረጋገጫና ምዝገባ ኤጀንሲ የተረጋገጠ የባለቤትነት ማረጋገጫ ውክልና ማቅረብ ይኖርባቸዋል። ተጨማሪ መረጃዎች መቅረብ ያለባቸው ሰነዶች በጨረታ ሰነዱ በተገለፀው ይሆናል። እንዲሁም ደስትቢን የደረቅ ቆሻሻ የሚለይበት ከረጢት /ማዳበሪያ/ ፣ የተለያዩ ህትመቶች እና የትራፊክ የአደጋ ምልክት (Traffic protective Cones) በፍላጎት መግለጫ መሰረት ጨረታው ከመከፈቱ በፊት ናሙና /ሳምፕል ማቅረብ የሚችል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ በተገለጸው ዋጋ የማይመለስ በጥሬ ገንዘብ በመክፈል ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ከጽዳት አስተዳደር ኤጀንሲ 9ኛ ፎቅ መግዛት ይችላሉ።
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታው ማስከበሪያ ዋስትና በባንክ የተረጋገጠ የክፍያ ማዘዣ (CPO) ወይም ከታወቀ ባንክ የቀረበ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና (Bid Bond) ከመጫረቻ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል። የሚቀርበው የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) ከሆነ በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ መሆን ይኖርባቸዋል።
- አሸናፊ ተጫራች የውል ማስከበሪያ ጠቅላላ ዋጋውን 10% (አስር በመቶ) በግዥ አፈፃጸም መመሪያ መሠረት ማስያዝ የሚችል
- ተጫራቾች ለጨረታው የሚያቀርቡት ሰነድ ፋይናንሻል እና ቴክኒካል ለየብቻው ለይተው በፖስታ አሽገው ስም እና አድራሻ በግልፅ በመፃፍ ለዚሁ ለተዘጋጀው ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን፡ ይህ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ 10 የስራ ቀናት ከቆየ በኋላ በ11ኛ የስራ ቀን ከጧቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በዚሁ ዕለት 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ቴክኒካል ሰነዱ በመንግሥት ግዥ ዳይሬክቶሬት 10ኛ ፎቅ ይከፈታል፡፡ ነገር ግን ጨረታ ሚከፈትበት ቀን ሕዝባዊ በዓል ወይም ቅዳሜ እና እሁድ ከሆነ ሌላ ማስታወቂያ ማውጣት ሳያስፈልግ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተጠቀሰው ሰዓትና ቦታ የሚከፈት ይሆናል።
- ኤጀንሲው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታው በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ማስታወሻ
የደረቅ ቆሻሻ መጣያ (ደስትቢን) ፤ የገረጋንቲና ቦልድ ድንጋይ እንዲሁም የህትመቶች ግዥዎች ዓመታዊ ግዥ ሲሆኑ ተጫራቾች ለአንድ ዓመት የዋጋ ለውጥ ሳይኖረው ውል ገብተው በግዥ ፈፃሚው አካል በሚፈልገው ጊዜ እና ወቅት በሚቀርበው የግዥ ትዕዛዝ የሚፈጸም ይሆናል። የኤጀንሲው አድራሻ፡ ፒያሳ በተለምዶ እሪ በከንቱ ተብሎ የሚጠራው ቀበሌ 15 ኢትዮ ሴራሚክስ ጎን ማዕከላዊ ስታቲስቲክስ ኤጀንሲ ፊት ለፊት ቢቲ ታዎር (ዮናታን ቢቲ ፈርኒቸር) ነው።
ስልክ ቁጥር፡- 251-011-275- 0002
የአዲስ አበባ ከተማ የፅዳት አስተዳደር ኤጀንሲ
