የየካ/ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ አስተዳደር ቡድን የ2018 በጀት አመት 1ኛ ዙር የስፖርት ትጥቅ ልብስ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
5ኛ ዙር 2017 ዓ.ም
የየካ/ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ አስተዳደር ቡድን የ2018 በጀት አመት 1ኛ ዙር የስፖርት ትጥቅ ልብስ ግዥ መፈፀም ይፈልጋል፤
ሎት 1 የስፖርት ትጥቅ ልብስ ግዥ (CPO-50,000)
ስለዚህ በጨረታ ላይ መሳተፍ የምትፈልጉ ሀጋዊ ተጫራቾች የሚከተሉትን መስፈርቶች በማሟላት እንድትጫረቱ ተጋብዛችኋል።
- የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የንግድ ምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የአቅራቢነት የምስክር ወረቀት ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነት እና የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ማስረጃ ኮፒ ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ናሙና እንዲቀርብ የተጠየቁባቸውን ዕቃዎች መጫረቻ ሠነዳቸውን ሲያስገቡ አብረው የተጠየቀውን ወይም የሚወዳደሩበትን ናሙና የማስገባት ግዴታ አለባቸው።
- የዘመኑን ግብር ስለመክፈላቸው ከሚመለከተው የገቢ ግብር ባለስልጣን ክሊራንስ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ሲፒኦ ከላይ በተገለፀው መሰረት በአዲስ አበባ ከተማ የየካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጽ/ቤት ስም የተዘጋጀ በባንክ ከተረጋገጠ ሲፒኦ ኦርጅናል ሰነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን ሲገዙ የማይመለስ ለአንዱ ሎት 200 (ሁለት መቶ ብር) በመክፈል መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በሚገባ በመሙላት ማስታወቂያው አየር ላይ ከዋለበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ የስራ ቀናት ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ውስጥ ኦርጅናል እና ኮፒ መሆኑን በመግለፅ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሳጥኑ በ11ኛው ቀን 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ እለት ከቀኑ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በመንግስት ግዥ አስተዳደር ቡድን ቢሮ ቁጥር 9 ውስጥ ተጫራቾች በሚያቀርቡት ዋጋ ስርዝ ድልዝ የሌለበት እና ቫትን ያካተተ መሆኑን አለመሆኑን ካልተገለፀ የቀረበው ዋጋ ቫት እንደተካተተ ተደርጎ ይወሰዳል፡፡
- ተጫራቾች ጨረታውን ሲያሸንፉ የውል ማስከበሪያ CPO 10% ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ያላሟላ የጨረታ ሰነድ ተቀባይነት የለውም።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው። ስልክ ቁጥር፡- 011-8-67-81-75
የየካ/ክ/ከተማ አስተዳደር ዋና ስራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት የመንግስት ግዥ ቡድን
