የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለህብረተሰቡ በሚደርሱ የእሀል አቅርቦቶች ላይ እሴት በመጨመር ለሸማች ማህበረሰብ ለማሰራጨት የእህል መፍጨት አገልግሎቱን የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ በማወዳደር ለአንድ ዓመት ውል በማስፈረም አገልግሎት ግዥ ለመፈጸም የመንግሥትን ግዥ መስፈርቶች የሚያሟሉ እና በዘርፉ ከተሰማሩ ሕጋዊ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የግዥ መለያ ቁጥር፡‐ ኢንሥኮ‐ ማእከል ግዥ ብ/ግ/ጨ/019/2017
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለህብረተሰቡ በሚደርሱ የእሀል አቅርቦቶች ላይ እሴት በመጨመር ለሸማች ማህበረሰብ ለማሰራጨት የእህል መፍጨት አገልግሎቱን የሚሰጡ ድርጅቶችን በግልጽ ጨረታ በማወዳደር ለአንድ ዓመት ውል በማስፈረም አገልግሎት ግዥ ለመፈጸም የመንግሥትን ግዥ መስፈርቶች የሚያሟሉ እና በዘርፉ ከተሰማሩ ሕጋዊ ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል፡፡
የተለያዩ የምርት ዓይነቶች (በቆሎ እና ጤፍ) እህል የመፍጨት አገልግሎት ግዥ፣ ስለሆነም በጨረታ ላይ መወዳደር የሚፈልጉ ድርጅቶች ከዚህ በታች የተጠቀሱትን መመዘኛዎች ማሟላት አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች የቴክኒክ ሰነዶችን 2017 ዓ.ም የታደሰ ንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ ምዘገባ ሰርተፊኬት፣ ወቅታዊ የግብር ክሊራንስ ሰርተፍኬት፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት እና የአቅራቢዎች ምዝገባ ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው። የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ማቅረብ የሚጠበቅባቸው ሲሆን እነዚህ ሰነዶች ፖስታ ውስጥ ታሽገው መቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ከላይ የተገለጹትን ሰነዶች ከጨረታ ሰነድ ማቅረቢያው ቀነ ገደብ በፊት ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ለሚወዳደሩበት ጨረታ የማይመለስ ብር 400.00 (ብር አራት መቶ) በመክፈል ከሐምሌ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ጀምሮ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00-6፡30 ሰዓት እንዲሁም ከሰእት ከ7:30-11:00 እንዲሁም ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡00 - 6፡30 ድረስ ብሎክ1 በቢሮ ቁጥር 206 ድረስ በመቅረብ መግዛት ይችላሉ፡፡ (አድራሻው ከስር ተገልጿል፡፡)
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን እስከ ጨረታው መዝጊያ ዕለት እስከ ሐምሌ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ከላይ ለተጠቀሰው ጨረታ የጨረታ ማስከበሪያ፡- ብር 10,000.00 (አስር ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስም አሠርተው ከጨረታ ሰነዳቸው ጋር ማቅረብ አለባቸው፡፡ ኢንሹራንስ ቦንድና ቼክ ተቀባይነት የላቸውም። የጨረታ ማስከበሪያው ፖስታ ውስጥ ወይም ለብቻው ታሽጎ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች አገልግሎት ዋጋ (ፋይናንሽያል)፣ ቴክኒካል ኦርጅናል በመለየት በአንድ ፖስታ በታሽገ ኤንቨሎፕ አሽገው ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ሐምሌ 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡30 ላይ ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ተጫራቶች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዋናው መሥሪያ ቤት የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ድርጅት የተለያዩ የምርት ዓይነቶች (በቆሎ፣ እና ጤፍ) በ5 ኪ.ግ 10 ኪግ፣ 15 ኪ.ግ 25ኪ.ግ እና በ50 ኪ.ግ እህል የመፍጨት አገልግሎት ግዥ ብር 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በሲፒኦ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና በኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን ስም አሠርተው ውሉን የሚፈጽሙ ይሆናል፡፡
- ኮርፖሬሽኑ ጨረታውን በከፊልም ወይም ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብረቱ የተጠበቀ ነው። ለማንኛውም ማብራሪያ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ በመደወል መጠየቅ ይቻላል፡፡
አድራሻ፡- ደብረዘይት መንገድ ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጠመንጃ ያዥ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት
ስልክ ቁጥር:- 011 416 73 45/011 466 9336
የኢትዮጵያ ንግድ ሥራዎች ኮርፖሬሽን
