ሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለሥራ አገልግሎት የሚውል ገልባጭ መኪና (Dump Truck) እና ፍላት ትራክ (Flat Truck) አቅራቢ ድርጅቶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ሀገር አቀፍ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
ቁጥር 03/2017
ሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን ለሥራ አገልግሎት የሚውል ገልባጭ መኪና (Dump Truck) እና ፍላት ትራክ (Flat Truck) አቅራቢ ድርጅቶችን በጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የሚችሉ ተጫራቾች በዘርፉ ተገቢ የሆነ የታደሰ ንግድ ፍቃድ ያላቸውና ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ፣ በጨረታ እንዲሳተፉ ከገቢዎች መ/ቤት የተሰጠ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
በጨረታው ለመሳተፍ የሚችሉ ተጫራቾች፡-
- በዘርፉ የአቅራቢነት የታደሰ ሕጋዊ ፍቃድ ያላቸው።
- ቫት ተመዝጋቢ የሆኑ።
- በጨረታ ለመሣተፍ ከገቢዎችና ከጉምሩክ ፍቃድ ያላቸው።
- የመልካም ሥራ አፈፃፀም ማስረጃ ያላቸው መሆን ይኖርባቸዋል፡፡
የጨረታ ሰነድ የሚሽጥበት ጊዜና ቦታ፡-
- ጨረታው ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 15 ተከታታይ ቀናት ድረስ የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን የሂሳብ ቁጥር 1000604259658 በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ገቢ በማድረግ የንግድ ፍቃዳቸውን ፎቶ ኮፒ ይዘው በመቅረብ የጨረታ ሰነድ መግዛት ይችላሉ፣
ጨረታው የሚከፈትበት እና ሰነዱ የሚቀርብበት ጊዜ፡-
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳቸውን ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ16ኛው ቀን ከቀኑ ከ8፡30 እስከ 11፡00 ሰዓት በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ያስገባሉ፡፡
- በማግስቱ በ17ኛው ቀን ከጠዋቱ በ3፡30 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- ዕለቱ የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይከፈታል።
የጨረታ ዋስትና፡-
- ማንኛዉም ተጫራች 2% በባንከ የተረጋገጠ CPO ወይም ከስድስት ወር ያላነሰ ጊዜ ያለው በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ ቢድ ቦንድ ዋስትና ከዋጋ ማቅረቢያ ጋር አያይዞ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡
የጨረታ ሠነድ አስተሻሸግ ሁኔታ፡-
- የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማስረጃ ፣ የልዩ እሴት ታክስ ተመዝጋቢነትና የታክስ ክፍያ ማረጋገጫ ሰነዶች፣ በጨረታው ለመሳተፍ ከገቢዎች የተሰጠ ማስረጃ እና የጨረታ ማስከበሪያ በባንክ የተደገፈ CPO/ ከኦርጂናል የዋጋ ማቅረቢያ ጋር በአንድ ላይ በሰም ታሽገው መቅረብ አለባቸው፡፡ ፋይናንሻል ዶክሜንት ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻ በሰም ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
- ቴክኒካል ዶክመንት ኦርጅናልና ኮፒ ለየብቻ በሰም ታሽጎ መቅረብ ይኖርበታል፡፡
ይህንን አስተሻሸግ ዘዴ ያልተጠቀመ ተጫራች ከጨረታው ይሠረዛል፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር 0916071539 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
ኮርፖሬሽኑ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ሲዳማ ኮንስትራክሽን ሥራዎች ኮርፖሬሽን (ሲኮስኮ)
