የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን አሰላ በሚገኘው ይዞታው ላይ የአሰላ ብቅል ፋብሪካ ግቢ ውስጥ የከብት መኖ ማቀነባበሪያ ማሽን መጋዘን ለማሰራት ሰነድ ላይ ባለው የሥራ ዝርዝር እና ቅድመ ሁኔታዎች (Evaluation criteria) መሰረት በዘርፉ ላይ የተሰማሩ ኮንትራክተሮች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን አሰላ በሚገኘው ይዞታው ላይ የአሰላ ብቅል ፋብሪካ ግቢ ውስጥ የከብት መኖ ማቀነባበሪያ ማሽን መጋዘን ለማሰራት ሰነድ ላይ ባለው የሥራ ዝርዝር እና ቅድመ ሁኔታዎች (Evaluation criteria) መሰረት በዘርፉ ላይ የተሰማሩ ኮንትራክተሮች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡
በመሆኑም በጨረታው ለመሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነጥቦች በማሟላት የጨረታ ሰነድ መውሰድ የምትችሉ መሆኑን ያሳውቃል።
- ጠቅላላ ሥራ ተቋራጭ ደረጃ 5 እና ከዚያ በላይ/ የህንፃ ሥራ ተቋራጭ ደረጃ 4 እና ከዚያ በላይ/ ፍቃድ ያለው።
- ተጫራቾች የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) በመክፈል ጨረታ ሰነዱን ከኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ይህ ጨረታ በማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21 ተከታታይ ቀናት ብቻ መውሰድ ይቻላል (የጨረታ ሰነድ ለመግዛት የስራ ቀናትን ከሰኞ - አርብ እንድትጠቀሙ እናሳስባለን)
- ተጫራቾች በዚህ የንግድ ዘርፍ የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ ቲን ቫት፤ የንግድ ምዝገባ እና ሰነድ ይሸጥልኝ ማመልከቻ ጋር ማቅረብ የሚችል፡፡
- ጨረታው የሚገባበት እና የሚከፈትበት በ22ኛው ቀን ሲሆን 22ኛው ቀን የስራ ቀን ካልሆነ ቀጥሎ ባለው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ተዘግቶ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በዚሁ ዕለት በ4፡30 ይከፈታል።
- ድርጅታችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ |ተጫራቹ ጥሩ የመልካም ስራ አፈፃፀም ሪከርድ ከሌለው ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ ለሙሉ የመሰረዝ መብት አለው፡፡
- ተጨማሪ ማብራሪያ ከድርጅቱ መረዳት ይቻላል።
- አድረሻ፡- ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ ጀሞ ሚካኤል አጠገብ የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን ዋና መ/ቤት “OACF Building” ላይ 6ተኛ ፎቅ የቢሮ ቁጥር 12
ስልክ፡-070 679 5079/ 09 10 64 54 42
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ሥራ ማህበራት ፌዴሬሽን
