Tender Detail

Tender Details

  • Company Felege Hiwot Comprehensive Specialized Hospital (የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል)
  • Address ባህርዳር ከተማ ቀበሌ 13፡ አማራ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0583205738
  • Websitehttps://felegehiwothospital.com
  • Deadline19 Aug 2025, 12:00 AM
  • magazine አዲስ ዘመን
  • Bid Document Price300.00
  • opening date2025-08-19 00:00:00
  • Categories Chemicals And Reagents , Printing And Publishing , Laboratory Equipment And Chemicals

የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል በ2018 በጀት ዓመት የተለያዩ የላብቶሪ ሪኤጀንቶችንና ሳፕላይስ እንዲሁም የተለያዩ የህትመት ሥራዎችን ከሚመለከታቸው ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል።


 

የጨረታ ማስታወቂያ

የጨረታ ቁጥር-//አጠ/ስፔ/ 005/18

 

የፈለገ ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 2018 በጀት ዓመት የተለያዩ የላብቶሪ ሪኤጀንቶችንና ሳፕላይስ እንዲሁም የተለያዩ የህትመት ሥራዎችን ከሚመለከታቸው ድርጅቶች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ግዥ ለመፈፀም ይፈልጋል።

በመሆኑም በዚህ ጨረታ የሚወዳደሩ ድርጅቶች፡-

  1. በዘመኑ የታደሰና በዘርፉ ሕጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው
  2. የግብር ከፋይነት መለያ /TIN CARD/ ሰርቴፊኬት ያላቸው
  3. አጠቃላይ የግዢ መጠን ከብር 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ አቅራቢው የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
  4. ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተ. 1- 3 የተጠቀሱትን የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶ ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው::
  5. አጠቃላይ ስለ ጨረታው ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ እና የጨረታ መመሪያ ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዟል፡፡
  6. ተጫራቾች በጨረታው የህትመት ሥራው ላይ ሙሉ በሙሉ መወዳደር ያለባቸው ሲሆን ሥራውን አሸናፊ የሆነው ድርጅት ለአንድ አመት ውል በመውሰድ ሆስፒታሉ በሚፈለገው ጊዜ በሚሰጠው የሥራ ትዕዛዝ መሰረት ሠርቶ ማቅረብ ይኖርበታል፡፡ በላብራቶሪ -ኤጀንትና ሰፕላይስ ላይ ተጫራቾች ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል መወዳደር ይችላሉ፡፡
  7. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 300.00 /ሶስት መቶ ብር/ ብቻ በመፈል ከሆስፒታሉ ዋና /ያዥ ቢሮ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 16 ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ማግኘት ይችላሉ፡፡
  8. ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት አቅርቦት የላብራቶሪ ሪኤጀንት ማንኛውንም ግብር እና ጨምሮ የሚሞሉትን ጠቅላላ ዋጋ 2% /ሁለት ፐርሰንት/ እና ለህትመት ሥራው 10,000.00 (አስር ብር) በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ (ፒኦ/ ወይም በሆስፒታሉ የጥሬ ገንዘብ መሰብሰቢያ ደረሰኝ ገቢ በማድረግ ዋናውን ደረሰኝ ከፖስታው ውስጥ አብረው ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡
  9. ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሃሳቡን በአማርኛ ቋንቋ ስርዝ ድልዝ ሳይኖር በዋጋ ማቅረቢያው መሰረት ንዱን ጠቅላላ ድምር ዋጋ በመሙላትና የድርጅቱን ህጋዊ ማህተም ፊርማና አድራሻ በማስቀመጥ በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በሆስፒታሉ አስተዳደር ህንፃ 4 ፎቅ የግዥ ፊሰሮች ቢሮ ቁጥር 9 /ዘጠኝ/ ለዚሁ ተብሎ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በሥራ ሰዓት ይህ ጨረታ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 16 ቀናት 4:00 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል ሳጥኑም በዚሁ ዕለት ከቀኑ 415 ይታሸጋል።
  10. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሆስፒታሉ ግዥ ኦፊሰሮች ቢሮ በዚሁ ቀን ከቀኑ 430 ሰዓት ይከፈታል፡፡ ቀኑ በዓል ዝግ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል፡፡
  11. ሆስፒታሉ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው
  12. በጨረታው የሚሳተፉ አካላት ስለጨረታው ዝርዝር መረጃ ማብራሪያ ከፈለጉ በአካል በመምጣት ወይም በስልክ ቁጥር 058 3205738 / 058 222 0916 በመደወል ማግኘት ይችላሉ፡፡

 

ህይወት አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል ባህር ዳር

 

Save Tender