Tender Detail

Tender Details

  • Company የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን (EBC)
  • Address ቸርችል ጎዳና፣ አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ, Phone: 0115172521
  • Websitehttps://www.ebc.et/about.aspx
  • Deadline10 Aug 2025, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price100.00
  • opening date2025-08-10 00:00:00
  • Categories Vehicle

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሀይብሪድ ተሸከርካሪ ግዥ በሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።


የግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ (NCB017/2017)

የኢትዮጵያ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን የሀይብሪድ ተሸከርካሪ ግዥ በሀገር አቀፍ ግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል። በዚህም መሰረት በጨረታ ላይ መሳተፍ የሚፈልጉና ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ሁሉ መወዳደር ይችላሉ።

  1. ተጫራቾች በዘርፉ የተሰማሩበት ህጋዊና የዘመኑን ግብር ከፍለው የታደሰ ንግድ ፍቃድ ፤በመንግስት ግዥ ላይ ለመሳተፍ የተመዘገቡበት የአቅራቢነት ምዝገባ ምስከር ወረቀት፤ የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር (ቲን) ምስከር ወረቀት፤ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፊኬት እና የግብር ክሊራንስ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፤
  2. ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ ብር ብቻ/ በመከፈል ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይቀናት ውስጥ ዘወትር በስራ ሰዓት ሸጎሌ በሚገኘው በኢትዮጵያ ብሮድ ካስቲንግ ኮርፖሬሽን ግዥ ዲፓርትመንት ቢሮ ድረስ በመምጣት መግዛት ይችላሉ።
  3. ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የሚሆን ብር30,000.00 (ሰላሳ ሺህ ብር) በባንክየተመሰከረለት ሲፒኦ ወይም በሁኔታዎች ላይ ያልተመሰረት ባንክ ጋራንቲ በኢትዮጵያ ብሮድካስቲን ኮርፖሬሽን ስም አሰርተው ከኦሪጅናል የቴክኒካል የመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
  4. ተጫራቾች የሚያቀርባቸውን የመወዳደሪያ ሰነዶች ፋይናንሺያል አንድ ኦሪጅናልና አንድ ኮፒ በፖስታ ለየብቻው አሽገው የጨረታውን ስምና ቁጥር በመፃፍ ማህተማቸውን በመምታት ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ተከታታይ ቀን ጀምሮ እስከ6ኛው ቀን ከቀኑ 815 ሰኣት ድረስ ብቻ በኮርፖሬሽኑ ግዥ ዲፓርትመንት ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሣጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል። 8 15 ሰኣት በኋላ ማለትም የጨረታ ሳጥኑ ከተዘጋ በኋላ የሚመጡ ተጫራቾች ተቀባይነት አይኖራቸውም
  5. ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ ቀናት 16ኛው ቀን ከቀኑ 815 ተዘግቶ በዚሁ ዕለት ከቀኑ 830 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሸጎሌ በሚገኘ በኮርፖሬሽኑ ዋናው /ቤት ግዥ ዲፓርትመንት ቢሮ ውስጥ ይክፈል። ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የመንግስት የሥራ ቀን ካልሆነ ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ ተዘግቶ የሚከፈት ይሆናል።
  6. ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ሸጎሌ በሚገኘው በኮርፖሬሽኑ ዋና /ቤት ግዥ ዲፓርትመንት ቢሮ ውስጥ ይከፈታል።
  7. ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የመንግስት የሥራ ቀን ካልሆነ ወይም ቅዳሜና እሁድ ከሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓትና ቦታ ተዘግቶ የሚከፈት ይሆናል።
  8. ተጫራቾች የጨረታውን ዝርዝር ሁኔታዎች ከጨረታ ሰነዱ ላይ የሚያገኙ ሲሆን ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልግ በስልክ ቁጥር 011-517-25-11 ደውለው ወይም በአካል መጠየቅ ይችላሉ፡፡
  9. ኮርፖሬሽኑ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታው በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

የኢትዮጵያ ብሮድስቲንግ ኮርፖሬሽን

Save Tender