Tender Detail

Tender Details

  • Company በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
  • Address በስልጤ ዞን ፡ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል መንግስት ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 046 882 0005
  • Website
  • Deadline26 Aug 2025, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price800.00
  • opening date2025-08-26 00:00:00
  • Categories Building Construction , Construction Works

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ከልል መንግሥት የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ በ2018 በጀት ዓመት ለሚያስገነባው የወራቤ ስቴዲያም ትሪቡን ግንባታ ለማስገንባት በመስኩ የተሰማሩ ተቋራጮችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡


 

የጨረታ ማስታወቂያ

 

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ከልል መንግሥት የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዞኑ ወጣቶችና ስፖርት መምሪያ 2018 በጀት ዓመት ለሚያስገነባው የወራቤ ስቴዲያም ትሪቡን ግንባታ ለማስገንባት በመስኩ የተሰማሩ ተቋራጮችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም ደረጃቸው G.C-5 /B.C-4 እና ከዛ በላይ የሆኑ፣

  • የዘመኑን ግብር አጠናቀው የከፈሉ፣
  • የተጨማሪ እሴት የምዝገባ ሰርተፊኬት የሚያቀርብ፣
  • የታደሰ የንግድ ፈቃድና የስራ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉ፣
  • የኮንስትራክሽንና ከተማ ልማት ሚኒስቴር የዘመኑን የምዝገባ ሰርተፊኬት የሚያቀርቡ፣
  • የጨረታ ዋስትና 300,000 (ሶስት መቶ ሺህ ብር) ማስያዝ የሚችሉ፣
  • የመስራት አቅም እንዳላቸው የሚገልፅ የወቅቱን የባን እስቴትመንት እና የስራ ልምድ ብቃት ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ፣
  • የኦዲት ሪፖርት እና የድርጅቱን አወቃቀርና ከዚህ በፊት የሰሯቸውን ሥራዎች የሚገልፅ የስራ ልምድ ማቅረብ የሚችሉ ተቋራጮች ሰነዱን ከስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር03 በመቅረብ ለሰነድ የማይመለስ ብር 800 /ስምንት መቶ ብር/ ብቻ በመፈል መግዛት የምትችሉ መሆኑን እያሳወቅን የጨረታ ሰነዱን ፋይናንሽያል ዶክመንቱን በሚገባ በመሙላት አንድ ኦርጂናል እና 2 ኮፒ ለየብቻ ቴክኒካል ዶክመንቱን አንድ ኦሪጂናል እና ሁለት ኮፒ ለየብቻ በታሸገ ኤንቨሎፕ በማድረግ ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከታተመበት ዕለት ጀምሮ ባሉት 21 ተከታታይ ቀናት በኋላ ባለው የስራ ቀን 800 ሰዓት ስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል። የጨረታ ሳጥኑ በዚሁ ዕለት 800 ሰዓት ታሽጎ ከቀኑ 830 ሰዓት መገኘት የሚፈልጉ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።

ማሳሰቢያ

  • ተጫራቾች ያቀረቡት የጨረታ ዋስትና ከተጠቀሰው ዋጋ አንሶ ከተገኘ ከጨረታው ይሰረዛሉ።
  • የተወዳዳሪ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው አለመገኘት የጨረታ መክፈቻ ቀኑን አይለውጡም።
  • መምሪያው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።

ለበለጠ መረጃ፡- ስልክ ቁጥር 0467710586 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል

 

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግሥት የስልጤ ዞን ፋይናንስ መምሪያ

 

Save Tender