የጅማ ግብርና ምርምር ማዕከል በአውሮፓ ህብረት ድጋፍ የቡናውን ዘርፍ ለመደገፍ በተሰጠው እርዳታ ከዚህ በታች የተገለጹትን የተለያዩ ነገሮች በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
ግጨ ቁ 01/2017
የጅማ ግብርና ምርምር ማዕከል በአውሮፓ ህብረት ድጋፍ የቡናውን ዘርፍ ለመደገፍ በተሰጠው እርዳታ ከዚህ በታች የተገለጹትን ማለትም፡-
ሎት 1 አላቂ የኮንስትራክሽንና የግንባታ ዕቃዎች ፣ የኤሌክትሪክ ቁሳቁሶች
ሎት 2 ቋሚ የላቦራቶሪ ዕቃ ኤር ኮንዲሽነሮችና ቬንትሌተሮች ወዘተ
ሎት 3 ለመስኖ መስመር ዝርጋታ የሚያገለግሉ የተለያዩ መገጣጠሚያዎችን በግልፅ ጨረታ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ ተጫራቾች:-
- የዘመኑን በዘርፉ የታደሰ የንግድ ስራ ፈቃድ ያላቸው፣
- የተጨማሪ እሴት ታከስ ተመዝጋቢ የሆኑበት ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፣
- በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን ግብር የመክፈል ግዴታቸውን የተወጡ ስለመሆናቸው ክሊራንስ ማቅረብ የሚችሉ፤
- የግብር መክፈያ መለያ ቁጥር /Tin Number/ ሰርተፊኬት ያላቸውና
- በመንግስት ግዢና ንብረት ባለስልጣን በአቅራቢዎች ዝርዝር ላይና በ(WebSite) የተመዘገቡ ስለመሆናቸው የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፣
ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ላይ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ የስራ ቀናት ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት እስከ ቀኑ 10፡30 ድረስ ባለው ጊዜ ውስጥ በመግዛት ለጨረታ ማስከበሪያ የሚውል ብር 10,000.00 /አስር ሺ ብር/ በባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ በጅማ ግብርና ምርምር ማዕከል ስም በማስያዝ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ መልኮ በሚገኘው የጅማ ግብርና ምርምር ማዕከል የግዢ የስራ ክፍል በመምጣት የማይመለስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ። /የአሸናፊዎች የዕቃ ማስረከቢያ ቦታ መልኮ በሚገኘው ዋና ማዕከል መሆኑን እንገልጻለን።
ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት መልኮ በሚገኘው የጅማ የመሰብሰቢያ አዳራሽ ነሀሴ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ይከፈታል።
በበለጠ ለመረዳት በስልክ ቁጥር 0474525561/0911749116 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የጅማ የግብርና ምርምር ማዕከል
