በአብከመ የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ለከሚሴ ከተማ አስተዳደር ሴክተር መ/ቤቶች ለ2018 በጀት አመት የመኪና ጎማ፣ ባትሪ እንዲሁም የመኪና ስፔር የመኪና መለዋወጫ እቃ /በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የመኪና ባትሪ እና ጎማ እንዲሁም የመኪና ስፔር /የመኪና መለዋወጫ እቃ ግዥ/
ብሄራዊ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
በአብከመ የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ለከሚሴ ከተማ አስተዳደር ሴክተር መ/ቤቶች ለ2018 በጀት አመት የመኪና ጎማ፣ ባትሪ እንዲሁም የመኪና ስፔር የመኪና መለዋወጫ እቃ /በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለሆነም በጨረታው ለመሳተፍ ፍቃደኛ የሆኑ ፡-
- ለስራው ሀጋዊ ፈቃድ ኖሯቸው የዘመኑን ግብር የከፈሉ፤ ለስራው የምዝገባ የምስከር ወረቀት ያላቸው፤የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN/ ያላቸው፤
- የጨረታው ሰነድ ከከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 7 በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት ጀምሮ ለ 15 ተከታታይ ቀናት ከላይ የተዘረዘሩትን መረጃዎች ዋናና ኮፒ በመያዝ ዘወትር በስራ ቀንና ሰዓት ለእያንዳንዱ ሰነድ የማይመለስ የኢትዮ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል የጨረታ ሰነዱን መውሰድ ይችላሉ።
- ተጫራቾች የጨረታውን ሰነድ ዋና እና ኮፒ በማድረግ በታሽገ ኤንቨሎፖች በአብክመ የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ለዚሁ ተግባር በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ታትሞ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለአስራ አምስት /15/ ቀን ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት እስከ 11፡00 ሰዓት ድረስ ባለው ጊዜ ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው በቀን 26/12/ 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 4:30 ላይ በግዢ/ፋይ/ንብ/አስ/ዋና የስራ ሂደት ቢሮ ተጫራቾች ወይንም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- ተጫራቾች ተመላሽ የሚደረግ የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና በሚያቀርቡት ጠቅላላ ዋጋ ላይ 1% (አንድ ፐርሰንት በጥሬ ገንዘብ ወይንም በባንክ ትእዛዝ /CPO/ ማስያዝ አለባቸው።
- የጨረታ አሸናፊ የሆነው ድርጅት ውል በሚዋዋልበት ጊዜ የውለታ ማስከበሪያ ከአጠቃላይ ድምር ዋጋ 10% ማስያዝ ይኖርበታል።
- መሥሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይንም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ፤ በከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት በግንባር በመቅረብ ወይንም በስልክ ቁጥር 033 554 0144 ደውለው መረዳት ይችላሉ።
የከሚሴ ከተማ አስተዳደር ገንዘብ ጽ/ቤት
