የደ/ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መገዘዝ ንግድና የማማከር ሥራዎች ኢንተርፕራይዝ ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን ሎት 1፡ የተለያዩ ያገለገሉ ማሽኖች፣ ያገለገሉ የመኪና ጎማዎችና ባትሪ እና የብረት ቀለም/431/ ሽያጭ፤ ሎት 2፡ የሰርገኛና ጥቁር ጤፍ ሰብል በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡
በድጋሜ የወጣ ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የደ/ብርሃን ዩኒቨርሲቲ መገዘዝ ንግድና የማማከር ሥራዎች ኢንተርፕራይዝ ከዚህ በታች በሎት የተዘረዘሩትን ማለትም፡-
ሎት 1፡ የተለያዩ ያገለገሉ ማሽኖች፣ ያገለገሉ የመኪና ጎማዎችና ባትሪ እና የብረት ቀለም /431/ ሽያጭ፤ ሎት 2፡ የሰርገኛና ጥቁር ጤፍ ሰብል በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባችኋል
- ተጫራቾች ግለሰብ ከሆኑ የቀበሌ ወይም ናሽናል መታወቂያ እንዲሁም የንግድ ድርጅት ከሆኑ የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድ ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር ሰርተፍኬት ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ ምዝገባ ሰርተፍኬት፣ የዘመኑን ግብር መክፈላቸውን የሚያረጋግጥ ከግብር ሰብሳቢው ባለሥልጣን የተሠጠ የምስክር ወረቀት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሎት 1 ብር 30,000.00 /ሠላሳ ሺህ/ ብር፣ ለሎት 2 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/ ከታወቀ ባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲፒኦ/ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 10 /አስር/ ተከታታይ ቀናት ውስጥ ዘወትር ከሰኞ እስከ አርብ በሥራ ሠዓት ከጠዋቱ 2፡30-10፡00 ድረስ እና ቅዳሜ ከጠዋቱ 2፡30-6:30 ድረስ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርስቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ በሚገኘው በኢንተርፕራይዙ ቢሮ በመምጣት ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ በመክፈል መውሰድ ይችላሉ፡
- ጨረታው የሚቆይበት ጊዜ ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ 10 ቀናት ውስጥ እስከ ጠዋቱ 4:00 ሰዓት ድረስ ብቻ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው የመወዳደሪያ ሃሳባቸውን የያዘ የዋጋ ሰነድ ዋናና ቅጅ ለየብቻው በታሸገ ኢንቨሎፕ በኢንተርፕራይዙ ቢሮ ለዚሁ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- አንድ ተጫራች በሁሉም ወይም በከፊል ወይም በአንድ እቃ ላይ መጫረት ይችላል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ማስታወቂያው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ በወጣበት በ10ኛው ቀን ሲሆን ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው እንዲሁም ጨረታውን መታዘብ የሚፈልግ ማንኛውም አካል በተገኙበት ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 በግልፅ ይከፈታል፡፡ የጨረታው መክፈቻ ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ታሽጎ 4፡30 በግልፅ ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በሌላ ተጫራች ዋጋ ላይ ተመሥርተው የመወዳደሪያ ዋጋ ማቅረብ አይችሉም፡፡
- የጨረታውን ውጤት ለአሸናፊና ለተሸናፊ ተጫራቾች በእኩል ጊዜ በጽሑፍ እንገልፃለን፡፡
- ኢንተርፕራይዙ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥራችን፡- +251911388194/ ደውለው መጠየቅ ይችላሉ
የደብረብርሃን ዩኒቨርሲቲ መገዘዝ ንግድና የማማከር ሥራዎች ኢንተርፕራይዝ
