የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የመምሪያውን የአጥር ጥገና እና የመጋዘን ግንባታ ሥራዎች ለማከናወን ተቋራጮችን አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡
የጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 3/2017-2018
የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ የመምሪያውን የአጥር ጥገና እና የመጋዘን ግንባታ ሥራዎች ለማከናወን ተቋራጮችን አወዳድሮ ማሠራት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ በጨረታው መወዳደር የሚፈልጉ ተጫራቾች በማመልከቻ ሲጠይቁ ማሟላት የሚገባቸው መስፈርቶች፡-
- ሕጋዊ ምዝገባ መረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉ
- ደረጃቸው BC/GC-5 እና ከዚያ በላይ ፍቃድ ያላቸው
- የዘመኑን የንግድ ፍቃድ ያደሱ ሆነው ዋናውንና ኮፒውን ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- የዘመኑን የኮንስትራክሽን ሚኒስቴር እና የቫት ተመዝጋቢ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የምትችሉ።
- በጨረታ መወዳደር የሚፈልጉ ተወዳዳሪዎች የሚገዙት የጨረታ ሰነድ ጠቅሰው በማመልከቻ ሲጠይቁ ተወካዮች ከሆኑ ከድርጅቱ ሕጋዊ ውክልና ይዘው መቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቾች ከላይ የተገለጹትን መስፈርት አሟልተው ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21ኛው ቀን 6፡00 ሰዓት ድረስ የማይመለስ ብር 500.00 / አምስት መቶ ብር/ በጉራጌ ዞን ገቢዎች በመክፈል ጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 18 ቀርበው መግዛት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታውን ቴክኒካል እና ፋይናንሻል ዶክመንት ሲያቀርቡ
ሀ/ ለቴክኒካል ዶክመንት አንድ ኦርጅናል እና ሁለት ፎቶግራፊከ ኮፒዎች እያንዳንዳቸውን በሰም በታሸገ የጨረታ ማስከበሪያ 150,000 /አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ ወይም bid bond የጨረታ ማስከበሪያዎች ከአሪጅናል ዶክመንት ጋር በማድረግ በማሸግ ሁሉንም በአንድ ትልቅ እናት ፖስታ በማሸግ (ቴክኒካል በሚል በመለየት)
ለ/ ለፋይናንሻል ዶክመንት አንድ አርጅናል እና ሁለት ፎቶግራፊክ ኮፒ በሰም በማሸግ ሁሉንም በአንድ ትልቅ እናት ፖስታ ውስጥ በማሸግ ፋይናንሻል በሚል በመለየት እስከ 21ኛው ቀን 8፡00 ሰዓት ድረስ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- የጨረታ ማስከበሪያ ብር 150,000 /አንድ መቶ ሃምሳ ሺህ ብር/ በባንክ በተረጋገጠ ሲፒአ ወይም የግዥ መመሪያ በሚፈቅደው ዋስትና ለ90 ቀንና ከዚያ በላይ ፀንቶ የሚቆይ በጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ ስም ተዘጋጅቶ ከሚያቀርቡት ከቴክኒካል ዶከመንት አርጅናል አብሮ መቅረብ አለበት፡፡
- ከተራ ቁጥር 1-8 የተጠቀሱት መስፈርቶች ሙሉ ለሙሉ ያላሟላ ተጫራች ከውድድሩ ውጪ ይሆናል፡፡
- የጨረታው ቴክኒካል ዶክመንት በ21ኛው ቀን በ8፡00 ሰዓት ታሽጎ በዚያኑ ቀን ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት 8፡30 ሰዓት ላይ በጉራጌ ዞን ፋይናስ መምሪያ ቢሮ ቁጥር 18 ውስጥ በይፋ ይከፈታል።
- የፋይናንሻል የፕሮጀከቱ ግንባታ ዋጋ ከቴክኒክ ግምገማ ውጤት በኋላ የቴክኒካል ግምገማውን ያለፉት ተጫራቾች ሰነድ ብቻ የጨረታ ኮሚቴው በማስታወቂያ በሚገለጸው ቀን ይከፈታል፡፡
- ተጫራቾች በሚያቀርቡት ሰነድ ላይ ስማቸውን፣ ፊርማቸውን እና አድራሻቸውን ማስፈርና የድርጅቱን ማህተም ማስቀመጥ አለባቸው።
- በጨረታ ሰነዱ ላይ ምንም አይነት ስርዝ ድልዝ መኖር የለበትም፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜና እሁድ የሕዝብ በዓል/ ላይ ከዋለ ጨረታው የሚከፈተው በሚቀጥለው የሥራ ቀን ከላይ በተጠቀሰው ሰዓት ይሆናል ፡።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ማሳሰቢያ፡-
በጉራጌ ዞን ከተማ ልማትና ኮንስትራከሽን መምሪያ ከሚመለከታቸው ፕሮጀክቶች ውስጥ በአፈጻጸማቸው ምክንያት የ3ተኛ ዙር ማስጠንቀቂያ የተሰጣቸው እና ውል ያቋረጡ ተቋራጮች መወዳደር አይችሉም፡፡
* በጨረታው ሂደት ውስጥ ተሻሽሎ የወጣው የከልሉ የግዥ መመሪያ ተግባራዊ የሚደረግ መሆኑን እንገልጻለን፡፡ ለበለጠ መረጃ መ/ቤቱ ድረስ በአካል በመቅረብ ወይም በስልክ ቁጥር 011-3300112 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የጉራጌ ዞን ፋይናንስ መምሪያ
