ሆራይዘን አዲስ ጎማ ማ/ኃላ/የተ/የግ/ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል።
የጨረታ ሽያጭ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር፡-01/2018
ሆራይዘን አዲስ ጎማ ማ/ኃላ/የተ/የግ/ማ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን በጨረታ አወዳድሮ መሸጥ ይፈልጋል፡-
- የክራሸር ሮለሮች፣
- ልዩ ልዩ ዕቃዎች፣
- ልዩ ልዩ ሽቦዎች፣
- ስኮርች ኮምፓወንድ፣
- የብረት ፍቅፋቂ፣ የብሮንዝ ፍቅፋቂ፣
- ብላደሮች፣
- ያገለገሉ መካኒካል ማሽንስና ስፔር፣
- ያገለገሉ የኤሌክትሪክ ሞተሮች፣
- የተቆረጡ ጎማዎች፣
በመሆኑም ፍላጎት ያላቸውን ተጫራቶች በሙሉ እንዲሳተፉ ይጋብዛል፡፡
በጨረታው መሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች የሚከተሉትን ማሟላት ይጠበቅባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸውና የዘመኑን ግብር የከፈሉ መሆን አለባቸው።
- የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ድረስ በሥራ ቀናት የማይመለስ ብር 300 /ሶስት መቶ ብር/ በመክፈል ከኩባንያው የምርት ሽያጭ ቢሮ መግዛት እና እቃዎቹን ማየት ይችላሉ፡፡
- ተጫራቾች መግዛት የሚፈልጓቸውን እቃዎች በዋጋ ማቅረቢያ ሰነድ ላይ የእያንዳንዱን ዋጋ ከተጨማሪ እሴት ታክስ በፊት በግልፅ ሞልተው፤ ሙሉ ስማቸውንና አድራሻቸውን ጽፈው ከፈረሙበት በኋላ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት እለት ጀምሮ እስከ መስከረም 24 ቀን 2018 ዓ.ም 4፡00 ሰዓት ድረስ ከሽያጭ ቢሮ ፊት ለፊት ባለው የጥበቃ በር ቁጥር 2 ቢሮ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡ የጨረታ ሣጥኑ በዚሁ እለት በ4፡05 ሰዓት ይታሸጋል፡፡ ጨረታው መስከረም 24 ቀን 2018 ዓም በ4፡20 ሰዓት ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በግልጽ ይከፈታል፡፡
- ድርጅቱ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ፡- ንብረት አስተዳደር መምሪያ ቢሮ
ስልክ ቁጥር፡- 011-4-42-15-55/234 ወይም 09-43-88-03-72 መጠየቅ ይቻላል፡፡
ሆራይዘን አዲስ ጎማ ማ/ኃ/የተ/የግ/ማ
