ቦሌ ማተሚያ ኃየተ.የግ.ማህበር ሎት 1 ለህትመት የሚሆኑ የተለያዩ ቀለሞች ሎት 2. የተለያዩ የጽዳት መጠቀሚያ ቁሳቁስ ሎት 3. የተለያዩ የስቴሽነሪ እቃዎችና የጽህፈት መሳሪያዎች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
የሀገር ውስጥ የግዥ ጨረታ ማስታወቂያ
ቦሌ ማተሚያ ኃየተ.የግ.ማህበር፡- ሎት 1 ለህትመት የሚሆኑ የተለያዩ ቀለሞች ሎት 2. የተለያዩ የጽዳት መጠቀሚያ ቁሳቁስ ሎት 3. የተለያዩ የስቴሽነሪ እቃዎችና የጽህፈት መሳሪያዎች በጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
- ተጫራቾች በዘርፉ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፣ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር፣ የቫት ተመዝጋቢ የምስክር ወረቀት፣ የንግድ ሰርቲፊኬት እና ሌሎችም የህጋዊነት ማረጋገጫ ሰነዶችን ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች በቅድሚያ የማይመለስ ብር 100.00 /አንድ መቶ/ ቢሮ ቁጥር 101 በመክፈል ለዚሁ ጨረታ የተዘጋጀውን ሰነድ ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 /አስራ አምስት/ ተከታታይ ቀናት ድረስ ቦሌ መንገድ ከቶታል ነዳጅ ማደያ ዝቅ ብሎ በሚገኘው ቢሮአችን መግዛት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ለጨረታ ማስከበሪያ የዋጋቸውን 2%፣ በባንክ በተረጋገጠ ቼክ /ሲፒኦ/ በቅድሚያ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ቴክኒካል እና ፋይናንሺል ሰነዶችን በአንድ ፖስታ አሽገው ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት ውስጥ ግዥ ክፍል በሚገኘው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ያስገባሉ።
- ተጫራቾች ለጥራት ሙከራ ይሆን ዘንድ ከሚጫረቱበት አይነት ናሙና /ሳምፕል/ ከሰነዶቻቸው ጋር አብሮ ማቅረብ ይጠበቅባቸዋል።
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባለው 15ኛው ቀን ከረፋዱ 3፡00 ሰዓት ላይ የጨረታ ሳጥኑ ታሽጎ በ3፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማህበሩ የስብሰባ አዳራሽ /የግዢ ክፍል/ ይከፈታል።
- ድርጅቱ ሌላ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
አድራሻ-
ቦሌ ማተሚያ ኃ/የተ/የግ/ማህበር
ስልክ ቁጥር …….. 01115 15 50 05/0115 51 88 72
ፋክስ …….. 0115 51 86 96
ፖ.ሳ.ቁ …….. 2365
ቦሌ መንገድ ከቶታል ነዳጅ ማደያ ዝቅ ብሎ
አዲስ አበባ
