በአብክመ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የስሪንቃ ግብርና ምርምር ማዕከል በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎታቸውን የጨረሱ የተከማቹ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች በሀራጅ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አሳውጆ ሽጦ ማስወገድ ይፈልጋል።
የሀራጅ ሽያጭ ግልፅ ጨረታ ማስታወቂያ
በአብክመ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የስሪንቃ ግብርና ምርምር ማዕከል በ2018 በጀት ዓመት አገልግሎታቸውን የጨረሱ የተከማቹ ቁርጥራጭ ብረታ ብረቶች በሀራጅ ጨረታ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ አሳውጆ ሽጦ ማስወገድ ይፈልጋል። በዚህም መሰረት በሎት 1 የተለያዩ ቁርጥራጭ የተከማቹ የተለያዩ መጠን ያላቸው ብረታብረቶች
ስለሆነም ተጫራቾች ለመሳታፍ የሚከተሉትን መስፈርቶች ማሟላት ይጠበቅባቸዋል።
- በስራ ዘርፍ ህጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያላቸው እና የዘመኑን ግብርየከፈሉ፡፡
- የቫት /የተጨማሪ እሴት ታክስ/ ተመዝጋቢ መሆናቸውን፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /Tin Number/ ያላቸው፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በስሪንቃ ግብርና ምርምር ማዕከል የግዥ ፋይናስ ንብረት አስተዳደር ቡድን የማይመለስ ብር 50.00 /አምሳ ብር/ በመክፈል ገዝተው መውሰድ ይችላላሉ፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን በትክክል ሞልተው በኦርጅናልና በኮፒ ሰነድ በ 2 በተለያየ ፖስታ አሽገው ለዚሁ የተዘጋጀ ሳጥን በየሎቱ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- የጨረታ ሰነዱን በሚመለከት በሎት 1 ያሉትን ከ15/01/2018 እስከ 29/01/2018 ዓ.ም እስከ ቀኑ 1፡30 ድረስ በመምጣት ገዝተው መውሰድ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ሳጥኑ የሚዘጋበት በ30/01/2018 ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ሲሆን በ4፡30 ይከፈታል። በጨረታው አይነት የሚመለከታቸው ተጫራቾች ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ሲሆን በጨረታው ያልተገኘ ተጫራች ፖስታው ተከፍቶ ለጨረታው ተገዥ ይሆናል /የመቀበል ግዴታ አለበት።
- ተጫራቾች ማንኛውንም ማስረጃዎች ሆነ ጥሬ ገንዘብ በእጅ ይዞ መቅረብ አይችሉም።
- ተጫራቾች ያሸነፋበትን ዋጋ ገቢ ሳያደርጉ እቃውን መውሰድ አይችሉም።
- የጨረታ ሳጥኑ ከታሸገ በኋላ የሚቀርብ ማስረጃ ተቀባይነት የሌለው ሲሆን የተሳሳተ ጨረታ ሰነድ ማቅረብ ከጨረታ ውጭ ያደርጋል በህግም ያስጠይቃል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን ቅዳሜና እሁድ ወይም በካላደር ዝግ ከሆነ የሚቀጥለው ስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
- ማንኛውም ተጫራች ጨረታውን የሚሞላው ከመነሻ ዋጋው በላይ መሆን አለበት። ንብረቱን በአካል ማየት አለባቸው።
- በጨረታው አሸናፊ ከሆነ የውል ማስከበሪያ ዋስትና ከጠቅላላ ዋጋ 5% (CPO) ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረት የባንክ ዋስትና ወይም ኢንሹራንስ ማስያዝ ይኖርበታል። ውሉም ሲጠናቀቅ ተመላሽ ይሆናል።
ማሳሰቢያ፡- ተጫራቾች ለበለጠ መረጃ 0333300090 /ሰሜን ወሎ ዞን ስሪንቃ /
በአብክመ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የስሪንቃ ግብርና ምርምር ማዕከል
