ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቬሎፕመንት /ECD/ በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ በፕሮጀክቱ በአጋር ትምህርት ቤቶች ላይ የተሰሩ ሥራዎችን በቪዲዮ እና በህትመት መልክ በመሰነድ ለልምድ ልውውጥ እና ለመማሪያ እንዲሁም ወደፊት ለሚቀርጹ ለሌሎች ፕሮጀክቶች እንደ ግብዓት እንዲያገለግል ለማድረግ ታቅዷል። በመሆኑም ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ላይ እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል።
የቪዲዮ ፕሮዳክሽን እና የመጽሔት ህትመት
ጨረታ ማስታወቂያ
ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቬሎፕመንት /ECD/ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በስድስት የአንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ ፔስታሎዚ የህናፃት መርጃ ድርጅት /PCF/ ከተባለ ዓለም አቀፍ አጋር ድርጅት ጋር በመሆን “Mobile Toolkit for Climate Resilience” የሚል ትኩረቱን በአየር ንብረት ለውጥ ላይ ያደረገ ፕሮጀክት በመተግበር ላይ ይገኛሉ፡፡ በመሆኑም በአየር ንብረት ለውጥ ዙሪያ በፕሮጀክቱ በአጋር ትምህርት ቤቶች ላይ የተሰሩ ሥራዎችን በቪዲዮ እና በህትመት መልክ በመሰነድ ለልምድ ልውውጥ እና ለመማሪያ እንዲሁም ወደፊት ለሚቀርጹ ለሌሎች ፕሮጀክቶች እንደ ግብዓት እንዲያገለግል ለማድረግ ታቅዷል።
በመሆኑም ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተወዳዳሪዎች በውድድሩ ላይ እንድትሳተፉ ተጋብዛችኋል።
- በዘርፉ የተሰማሩ መሆኑን የሚገልጽ ለዘመኑ የታደሰ የንግድ ፍቃድ ማቅረብ የሚችሉ፣
- ቲን ነምበር ሰርተፊኬት ማቅረብ የሚችሉ፣
- የቫት ተመዝጋቢ የሆኑና ሰርተፊኬቱን ማቅረብ የሚችሉ፣
- በቪዲዮ ፕሮዳክሽን እና ህትመት ሥራ ልምድ ያላቸው፣ እንዲሁም
- ከዚህ ቀደም ተመሳሳይ ሥራዎች መሥራታቸውን የሚያሳይ የሥራ ልምድ ማቅረብ የሚችሉ፣
ከላይ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ተጫራቾች ይህ የጨረታ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከታወጀበት እለት አንስቶ ለ5 (አምስት) ተከታታይ የሥራ ቀናት ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቬሎፕመንት /ECD/ ቢሮ በመምጣት የጨረታውን ሰነድ በነጻ በመውሰድ የቪዲዮ ፕሮዳክሽኑን እና ህትመቱን የምትሰሩበትን ዋጋ በመሙላት በታሸገ ኤንቨሎፕ ገቢ አድርጋችሁ እንድትወዳደሩ እንገልፃለን።
አድራሻ፡ -ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዲቨሎፕመንት /ECD/
ቦሌ አለም ህንፃ 7ኛ ፎቅ
ስልክ፡- 0982 882 826
አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ማሳሰቢያ፡-
- ተጫራቾች የምታቀርቡት ዋጋ ቫትን ያካተተ መሆን አለመሆኑን በግልጽ ማሳየት ይኖርባችኋል፡፡ በትክክል ካልተገለጸ ዋጋው ቫት እንደተካተተ ተደረጎ ይቆጠራል።
- ድርጅታችን የተሻለ አማራጭ ካገኘ ያለ ምንም ቅድመ ማስጠንቀቂያ እና ማስታወቂያ ጨረታውን ሙሉ በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ኢትዮጵያን ሴንተር ፎር ዴቨሎፕመንት
