የፈዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት የግንባታ ስራ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
የጨረታ ማስታወቂያ
የፈዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን በ2018 በጀት ዓመት የግንባታ ስራ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል።
|
ተ/ቁ |
የስራ ዓይነት |
|
1 |
የአጥር፣ የዋና መግቢያ በር እና ህንጻዎች ቀለም ስራ |
በመሆኑም በጨረታው መሳተፍ የምትፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ ቀጥሎ የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባችሁ፡፡
- በዘርፉ ህጋዊ ንግድ ፈቃድ ያላቸው መሆን በዘርፉ የተሰማሩ ለመሆናቸው በጀርባው የተገለጸ መሆን አለባቸው።
- የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉ፤
- ተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ፤ የታደሰ የዘመኑ ንግድ ፈቃድ ማቅረብ የሚችሉና የታደሰ የንግድ ምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የመንግስት መ/ቤቶች ለሚያወጡት ጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል የአቅራቢዎች የምዝገባ ሰርተፊኬት ማቅረብ አላቸው፡፡ እንዲሁም በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ከገቢዎች ባለስልጣን የዘመኑን ግብር ከፍለው ስለማጠናቀቃቸው ማስረጃ ማቅረብ አለባቸው፡፡
- አማራጭ ዋጋ በዚህ ጨረታ ማቅረብ አይቻልም፡፡
- በጨረታ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ሁሉ የጨረታ ውጤቱ እንደታወቀ ተመላሽ የሚሆን የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ተብሎ በተዘጋጀው ከባንክ በተመሰከረበት ሲፒኦ 500,000 /አምስት መቶ ሺህ ብር/ ማስያዝ ይኖርባቸዋል፡፡ እንዲሁም የባንክ ዋስትና የሚያስይዙ ተጫራቾች የቆይታ ጊዜው ጨረታው ከተከፈተበት ቀን ጀምሮ የሚቀጠር 118 ቀን መሆን ይኖርበታል፡፡
- ተጫራቾች ቴክኒካል ሰነዶችና የዋጋ ማቅረቢያዎችን /ፋይናንሻል/ ሰነዶችን በተለያዩ ፖስታ ታሽጎ ለየብቻ መቅረብ አለበት፡፡ ቴክኒካል ፋይናንሻል ሰነድ በአንድ ላይ አሽጎ ያቀረበ ተወዳዳሪ ያለምንም ቅድመ ሁኔታ ከጨረታው ውጭ ይደረጋል፡፡
- ማንኛውም ተጫራቶች የሚያስገባው ሰነድ ፋይናንሻል የጨረታ ሰነድ አንድ አሪጅናልና አንድ ኮፒ በተለያዩ ፖስታ በሰም በማሸግ በፖስታው ላይ የጨረታ ሰነዱን ቁጥር የሚጫረትበትን በትክክል መጻፍ እንዲሁም በፖስታው ላይ እና በሁሉም የመጫረቻ ሰነድ ላይ የድርጅቱን ማህተም በመምታት ማስገባት ያለበት ሲሆን ስርዝ ድልዝ በፍሉድ የጠፋ ሰነድ ዋጋ ያልተሞላበት ዝርዝር ተቀባይነት የለውም፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ የሚያሲዙት ሲፒኦ ከቴክኒክ ሰነዶች ጋር በአንድ ላይ ታሽገው መቅረብ አለባቸው፡፡
- ተጫራቾች አዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ፖሊስ ኮሚሽን ከፍ ብሎ በሚገኘው ፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን ዋናው መ/ቤት 1ኛ ፎቅ የፋይናንስ ቢሮ ቀርበው በእያንዳንዱ የጨረታ ሰነድ የማይመሰስ ብር 500.00 /አምስት መቶ ብር/ በመክፈል መግዛት ይችላሉ፡፡
- ጨረታው በ26/2/2018 ዓ.ም 6፡00 ሰዓት ታሽጎ በ8፡00 ሰዓት ሲሆን በመ/ቤቱ መሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል፡፡
- ዘግይተው የሚመጡ የጨረታ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ በከፊልም ሆነ በሙሉ ጨረታውን የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች የሚወዳደሩባቸውን የስራ አይነቶች ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 011-1-26-56-65 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡
የፌዴራል ማረሚያ ቤት ኮሚሽን
