የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃላ/የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን ነገሮች ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ በመጋበዝ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል።
ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃላ/የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ፡-
- LOT 1- Workshop Materials - NCB/OACFLTD/AMF/01/2018
- LOT 2- Electrical Materials - NCB/OACFLTD/AMF/02/2018
- LOT 3- Electrical and Mechanical tools - NCB/OACFLTD/AMF/03/2018
- LOT 4- Bearing-NCB/OACFLTD/AMF/04/2018
- LOT 5- Mechanical Seal and Oil Seal - NCB/OACFLTD/AMF/05/2018
- LOT 6- Sheet Metals and Angle Iron - NCB/OACFLTD/AMF/06/2018
- LOT 7- Steam Valves and pipe -NCB/OACFLTD/AMF/07/2018
ተጫራቾችን በግልፅ ጨረታ በመጋበዝ አወዳድሮ ለመግዛት ይፈልጋል። ስለሆነም በጨረታው ለመወዳደር የሚፈልጉ ድርጅቶች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ማሟላት አለባቸው።
- ተጫራቾች የዘመኑ የታደሰ የንግድ ፈቃድ፤ በግዥና ንብረት አስተዳደር ኤጀንሲ በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ፤ የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር /TIN) ያላቸው እና የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ተመዝጋቢ ስለመሆናቸው ሕጋዊ ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ መሆን ይኖርባቸዋል።
- የጨረታ ሰነዱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ የማይመለስ ብር 500.00 (አምስት መቶ ብር) ብቻ በፋብሪካችን አካውንት በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ 1000257808697 ወይም በኦሮሚያ ህብረት ስራ ባንክ 1000043405229 በመክፈል /ገቢ በማድረግ/ ዘወትር በስራ ሰዓት ከሰኞ እስከ ዓርብ ከ2፡00-6፡00 ሰዓት፤ ከሰዓት በኋላ 7:00-10፡00 ሰዓት ድረስ ከጀርመን አደባባይ ወደ ሚካኤል አደባባይ በሚወስደው መንገድ ላይ ሚካኤል ቤ/ክርስቲያን አጠገብ በሚገኘው የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ህንፃ ስድስተኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 6 ወይም አሰላ – ቁሉምሳ ከሚገኘው ፋብሪካችን ቢሮ ቁጥር 003 ሰነዱን መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች የመጫረቻ ሰነዳቸውን በፖስታ በማሸግ አዲስ አበባ በሚገኘው የፋብሪካችን ዋና መ/ቤት ለዚሁ ተበሎ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ከተጠቀሰው የመዝጊያ ሰዓት በፊት ማስገባት ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች ከመወዳደሪያ ሰነዳቸው ጋር የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለLOT 1 ብር 15,000.00፤ ለLOT 2 ብር 15,000.00፤ ለLOT 3 ብር 10,000.00፤ ለLOT 4 ብር 10,000.00፤ ለLOT 5 ብር 5,000.00፤ ለLOT 6 ብር 10,000.00፤ ለLOT 7 ብር 10,000.00 በባንክ በተመሰከረለት ሲፒኦ (CPO) ለየብቻ በማስያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን የጨረታ ማስታወቂያው ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለተከታታይ 21 ቀናት ክፍት ሆኖ የሚቆይ ሲሆን በ22ኛው ቀን LOT 1 እና LOT 2 በ4:00 ሰዓት ተዘግቶ በ4፡30 ሰዓት ላይ፤ LOT 3 እና LOT 4 በ5:00 ሰዓት ተዘግቶ በ5፡30 ሰዓት ላይ፤ LOT 5 LOT 6 እና LOT 7 ልክ በ5:40 ሰዓት ላይ ተዘግቶ በ 6፡10 ሰዓት ላይ ለመገኘት በሚሹ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት አዲስ አበባ በሚገኘው የፋብሪካችን ዋና መ/ቤት የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃላ/የተ ሰባተኛ ፎቅ ላይ በሚገኘው የመሰብሰቢያ አዳራሽ ይከፈታል። የመክፈቻው ቀን ቅዳሜ እና እሁድ ወይም የበዓል ቀን ከሆነ በሚቀጥለው የስራ ቀን በተመሳሳይ ሰዓት ይከፈታል።
- ፋብሪካው የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ተጫራቾች በጨረታ ማስታወቂያና በተጫራቾች መመሪያ ላይ ግልጽ ያልሆነ ነጥብ ካለና ተጨማሪ ማብራሪያ ከፈለጉ በስልክ ቁጥር 09-65-65-04-81/ 09-65-65-02-85 በሥራ ሰዓት ደውለው መጠየቅ ይችላሉ።
የኦሮሚያ ግብርና ህብረት ስራ ማህበራት ፌዴሬሽን ኃላ/የተ አሰላ ብቅል ፋብሪካ
