ኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ደቡብ ምስራቅ ሪጅን ጽ/ቤት ከታች በሰንጠረዥ በተገለፀው መሰረት ለመኪና ኪራይ አገልግሎት ከታች በተገለጸው መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
የመኪና ኪራይ አገልግሎት ጨረታ ማስታወቂያ
ኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ደቡብ ምስራቅ ሪጅን ጽ/ቤት ከታች በሰንጠረዥ በተገለፀው መሰረት ለመኪና ኪራይ አገልግሎት ከታች በተገለጸው መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለሆነም በዘርፉ የስራ ፈቃድ ያላችሁ እና ከታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች የምታሟሉ ድርጅቶች ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ 15 ተከታታይ ቀናት የጨረታ ሰነዱን ከባል ሮቤ ዋናው ጽ/ቤት ቢሮ ቁጥር 105 በመቅረብ የማይመለስ 200 ብር ከፍለው ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡ በተጨማሪም በኦንላይን www.merkato.com, www.afrotened-er.com and www.extratender.com መግዛት ይችላሉ።
|
የስራው አይነት |
የስራው ቦታ |
የጨረታው መለያ ቁጥር |
ጨረታው የሚጀመርበት ቀን |
የጨረታው የሚቆይበት ጊዜ |
የጨረታው መዝጊያ ቀን እና ሰዓት |
የጨረታው መክፈቻ ቀን እና ሰዓት |
የጨረታው ማስከበሪያ መጠን በብር |
|
የመኪና ኪራይ አገልግሎት |
ባሌ ሮቤ ሪጅን ጽ/ቤት |
4278393 |
ጥቅምት 13 ቀን 2018 ዓ.ም ከጠዋቱ 02፡30 ሰዓት |
15 ቀናት |
ጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 08፡00 ሰዓት |
ጥቅምት 28 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 08፡30 ሰዓት |
50,000 |
መስፈርቶች፡-
- የጨረታ ማስከበሪያ 50,000.00 (ሃምሳ ሺህ ብር) በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ ማቅረብ የሚችል
- የዘመኑን ግብር የከፈለ እና የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለው፣
- የቫት እና የቲን ሰርተፍኬት ማቅረብ የሚችል፣
- በገቢዎች አስተዳደር ባለስልጣን በጨረታ ላይ መሳተፍ የሚያስችል ደብዳቤ ያለው እና ደብዳቤውን ማቅረብ የሚችል፣
- አንድ የመልካም ስራ አፈጻጸም ማቅረብ የሚችል
- ተጫራቾች፡- ፋይናንሻል ዋናው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ቴክኒካል ዶክመንት ዋናው በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ ፋይናንሻል ኮፒውን በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ (ሁለት ኮፒ) ቴክኒካል ዶክመንት ኮፒውን (ሁለት ኮፒ) በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ እንዲሁም ሲፒኦ ለየበቻ አድርገው በአንድ እናት ፖስታ በማድረግ ለዚሁ በተዘጋጀ ሳጥን ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- መስሪያ ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡
ኢትዮ ቴሌኮም ደቡብ ደቡብ ምስራቅ ሪጅን
