የጌዴኦ ልማት ማህበር በዲላ ከተማ ለማሠራት ላቀደው የB+G+7 ህንጻ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ህጋዊ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል።
የግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ
የጌዴኦ ልማት ማህበር በዲላ ከተማ ለማሠራት ላቀደው የB+G+7 ህንጻ የመጀመሪያ ምዕራፍ ግንባታ ህጋዊ ተጫራቾችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለማሠራት ይፈልጋል።
በዚሁ መሠረት፡
- ደረጃቸው GG-4/BC-3 እና ከዚያ በላይ የሆኑ ተጫራቾች የ2017 ዓ.ም ፈቃዳቸውን ያሳደሱና የዘመኑን ግብር የከፈሉ፣ በኮንስትራክሽን ሚ/ር ወይም አግባበነት ካለው መንግሥት ተቋም የታደሰ የብቃት ማረጋገጫ ማቅረብ የሚችሉና የተጨማሪ እሴት ታክስ ተመዝጋቢ የሆኑ።
- ተጫራቾች ህጋዊ ፈቃዳቸውን፣ የተ.እ.ታ. የተመዘገቡበትን ሰርተፊኬትና የታክስ ክሊራንስ በማቅረብ የጨረታ ዶክመንቱን ይህ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን አንስቶ ባሉት 15 ተከታታይ ቀናት የማይመለስ ብር 1,000 /አንድ ሺህ ብር/ ብቻ በመክፈል ከጌዴኦ ልማት ማህበር ዲላ ቢሮ መግዛት ይችላሉ።
- ተጫራቾች አስፈላጊውን የሰው ሀይል፣ የሥራ መሳሪያዎችን እና ማሽነሪዎችን በግላቸው አቅርበው ግንባታውን መሥራትና ማጠናቀቅ ያለባቸው ሲሆን ድርጅታችን አስፈላጊ የግንባታ ግብዓቶችን የሚያቀርብ ይሆናል፡፡
- የጨረታ ማስከበሪያ/ቢድ ቦንድ ብር 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር ብቻ/ በሲፒኦ ወይም በባንክ ጋራንቲ ከመጫረቻ ሠነድ ጋር ማቅረብ ይኖርባቸዋል፡፡ ከዚህ ውጪ በኢንሹራንስ ወይም በሌላ መልኩ የሚቀርብ የጨረታ ማስከበሪያ ተቀባይነት የለውም።
- የጨረታው ሠነድ በተጫራቶች መመሪያ መሠረት ተሞልቶ የጨረታ ማስከበሪያ ለብቻ የፋይናንሻል ኦርጂናል እና ሁለት ፎቶ ኮፒ እንዲሁም ቴክኒካል ኦርጂናል እና ሁለት ፎቶ ኮፒዎችን ለየብቻቸው በማሸግ፣ በሁሉም ዶክመንቶች ላይ ህጋዊ ማህተም በማሳረፍና ስምና አድራሻ በመፃፍ ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ዕለት አንስቶ በ16ኛ ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ድረስ በጌዴኦ ልማት ማህበር ለዚሁ አገልግሎት በተዘጋጀ ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይገባቸዋል። 16ኛው ቀን የሥራ ቀን ካልሆነ የጨረታው ሠነድ በሚቀጥለው የሥራ ቀን በተመሣሣይ ሰዓት የሚገባ ይሆናል።
- የጨረታውን ሰነድ የያዘው ሣጥን በዚሁ ዕለት ከጠዋቱ 4:30 ላይ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት የሚከፈት ይሆናል።
- በዞኑና አካባቢዋ የግንባታ ሥራ አከናውነው መልካም አፈጻጸም ያላቸው ተጫራቾች ይበረታታሉ፡፡
- አሠሪው መ/ቤት የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- ለበለጠ መረጃ በስ.ቁ 0463314375 ደውሎ መጠየቅ ይቻላል፡፡
የጌዴኦ ልማት ማህበር
ዲላ
