የወሊሶ ከተማ /ጽ/ቤት በ2018 የበጀት አመት በወሊሶ ከተማ ወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት በመደበኛ በጀት የወሊሶ ከተማ እስታድዮም ጥገና ሥራን የኦሮሚያ ክልል መንግስት ባወጣው የመንግስት ግዥ አዋጅ ቁጥር 157/2002 እና የግዥ አፈጻጸም መመሪያን በመከተል በግልፅ ጨረታ ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
የግንባታ ጨረታ ማስታወቂያ
የጨረታ ቁጥር Waliso-SR-Main-002-CW-2018
የወሊሶ ከተማ /ጽ/ቤት በ2018 የበጀት አመት በወሊሶ ከተማ ወጣቶች እና ስፖርት ጽ/ቤት በመደበኛ በጀት የወሊሶ ከተማ እስታድዮም ጥገና ሥራን የኦሮሚያ ክልል መንግስት ባወጣው የመንግስት ግዥ አዋጅ ቁጥር 157/2002 እና የግዥ አፈጻጸም መመሪያን በመከተል በግልፅ ጨረታ ተቋራጮችን አወዳድሮ ለማሰራት ይፈልጋል፡፡
ዝርዝር ሁኔታዎች፡-
ጨረታው የሚቆይበት ጊዜ በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስክ 21ኛ ተከታታይ የስራ ቀን ድረስ ይሆናል። ተጫራቾች ለእስታድየም ጥገና ሥራ የተዘጋጀውን ሰነድ የማይመለስ ብር 1,000.00 (አንድ ሺህ የኢትዮጵያ ብር) በሲንቄ ባንክ በወሊሶ ከተማ ገ/ጽ/ቤት ሒሳብ ቁጥር 1071027311218 በማስገባት በወሊሶ ከተማ ገቢ ጽ/ቤት ደረሰኝ በመቁረጥ ከታደሰ ንግድ ፈቃድ ጋር ይዘው በመቅረብ ዘወትር በሥራ ሰዓት የወሊሶ ከተማ ገንዘብ ጽ/ቤት 3ኛ ፎቅ ከቢሮ ቁጥር 26 የጨረታ ሰነዱን መግዛት ይችላሉ፡፡
የተጫራቾች ግዴታዎች፡-
- በዘርፉ ሕጋዊ የታደሰ ንግድ ፈቃድ ያለቸውና የዘመኑን ግብር ከፍሎ ፈቃድ ያሳደሱ፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN NO) ያላቸው፣ በግንባታ ዲዛይን ቁጥጥር ባለስልጣን የተሰጠ ደረጃ GC-5 እና ከዚያ በላይ ያለው፣ የአቅራቢነት ምዝገባ ምስክር ወረቀት እና የቫት ተመዝጋቢነት ምስክር ወረቀት ያለውና የሚያቀርብ።
- ተጫራቾች የጨረታ መስከበሪያ ለጠቅላላ ግዥ ሕጋዊ ከሆነ ባንክ የተረጋገጠ CPO 400,000.00 (አራት መቶ ሺህ የኢትዮጵያ ብር) ኦርጂናሉን ከኦርጅናል ሰነድ ጋር አሽገው ማቅረብ አለባቸው።
- ተጫራቹ ከማጭበርበር፣ ከሙስና፣ ከማታለልና ከማስገደድ ድርጊት የማይፈጽሙ መሆኑን ለማረጋገጥ ግዴታ ለመግባት ከጨረታ ሰነዱ ጋር ተያይዞ የሚገኘውን ቅጽ ሞልተው በመፈረም ማስገባት አለባቸው፡፡
- የጨረታው አሸናፊው አሸናፊነቱ ከታወቀበት ቀን እንስቶ በ15 ቀናት ውስጥ ቀርቦ የውል ማስከበሪያ ዋስትና ያሸነፈበትን ዋጋ 10% በማስያዝ ውል ባይገባ ለጨረታ ማስከበሪያ ያስየዘው ገንዘብ ለመንግስት ውርስ ሆኖ በግዥ አዋጅ እና አፈጸጸም መመሪያ መሰረት ሕጋዊ እርምጃ ይወሰዳል፡፡ የውል ማስከበሪያ ዋስትናው ሕጋዊ ከሆነ ባንክ የተረጋጋጠ CPO የሚያስዝ እና ውል የገቡበትን ሥራ አጠነቀው እስኪጨርሱ ድረስ ፀንቶ የሚቆይ ይሆናል፡፡
- ተጫራቾች የመልካም ሥራ አፈጸጸም እና ሥራ ልምድ ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ጨረታው በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ እስከ 21ኛው ተከታታይ የስራ ቀን በአየር ላይ የሚውልበት ቀን በመሆኑ ተጫራቾች የሚወዳደሩበትን ዋጋ ያለ ስርዝ ድልዝ በጨረታ ሰነዱ ላይ በመሙላት ሁሉንም ማስረጃ እና በጨረታ ሰነድ ውስጥ በተገለፀው መሰረት የቴክኒክ እና የፋይናሻል ሰነድ አንድ ኦርጅናል እና ከሁለት ኮፒ ጋር በተላያየ ኤንቨሎፕ በማሸግ በወሊሶ ከተማ ገ/ጽ/ቤት 3ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 26 ለዚህ በተዘጋጀው ሣጥን ውስጥ ማስገባት ይችላሉ፡፡ ጨረታው በ22ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ተዘግተው በዕለቱ ከጠዋቱ 4፡30 ሰዓት ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡ ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው ሳይገኙ ቢቀሩ የጨረታውን የመክፈቻ ስነ ስርዓት አያስተጓጉልም፡፡
- ተጫራች ከዚህ በፊት ተመሳሳይ ሥራ ወስዶ ያስተጓጎለ፣ ያቋረጠ ያለበቂ ምክንያት ያዘገያ፣ እንዲሁም ከአሰሪው መ/ቤት በመሰል ተግባራት ማስጠንቀቂያ የተሰጠው ቅጣት የተጣለበት፤ ውል ያቋረጣ ተቋራጭ በቀጥታ ከውድድሩም ሆነ ከጨረታው ይሰረዛል፡፡
- ጨረታው የሚከፈትበት ቀን በዓል ከሆነ ጨረታው በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ቦታና ሰዓት ይከፈታል።
- ጽ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ከገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለተጨማሪ መረጃ በስልክ ቁጥር:- (011-341-3012/2108) በመደወል መጠያቅ ይችላሉ፡፡
የወሊሶ ከተማ ገንዘብ ጽ/ቤት
ወሊሶ
