በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን የበረኸት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል እቃ እና አገልግሎት፡ - ሎት 1 እስቴሽነሪ ፣ ሎት2 ኤሌክትሮኒክስ፣ ሎት 3 የእንሰሳት መድሀኒትና የህክምና እቃዎች ሎት የተሸከርካሪ ጎማ ሎት 5. የግንባታ እቃዎች ሎት 6. የፅዳት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ ቁጥር 01/2018
በአማራ ብሔራዊ ክልላዊ መንግስት በሰሜን ሸዋ ዞን የበረኸት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት ለሴ/መ/ቤቶች አገልግሎት የሚውል እቃ እና አገልግሎት፡ - ሎት 1 እስቴሽነሪ ፣ ሎት2 ኤሌክትሮኒክስ፣ ሎት 3 የእንሰሳት መድሀኒትና የህክምና እቃዎች፣ ሎት የተሸከርካሪ ጎማ ሎት 5. የግንባታ እቃዎች ሎት 6. የፅዳት ዕቃዎች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ ስለዚህ የሚከተሉትን መስፈርቶች የሚያሟሉ ተጫራቾች እንዲወዳደሩ ይጋብዛል፡፡
- በዘመኑ የታደሰ ህጋዊ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፡፡
- የግብር ከፋይ መለያ ቁጥር (TIN) ያላቸው።
- የንግድ ምዝገባ ምስክር ወረቀት ያላቸው
- የሚሞሉት ዋጋ ከብር 200,000.00 /ሁለት መቶ ሺህ ብር/ በላይ ከሆነ የተጨማሪ እሴት ታክስ /VAT/ ከፋይነት የተመዘገቡ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡
- ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተ.ቁ 1-4 የተጠቀሱትንና የሚመለከታቸውን ማስረጃዎች ፎቶኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡
- የሚገዙ ዕቃዎችን ዓይነትና ዝርዝር መግለጫ /ስፔስፊኬሽን/ ከጨረታ ሰነዱ ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዱን የማይመለስ ብር 100 /አንድ መቶ ብር/ ብቻ በመክፈል ከግ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 ማግኘት ይቻላል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና /ቢድ ቦንድ/ ለሚወዳደሩበት ለእስቴሽነሪ 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ ብቻ፤ ለኤሌክትሮኒክስ 20,000 /ሃያ ሺህ ብር/ ብቻ፣ የእንስሳት መድሀኒትና የህክምና እቃዎች 25,000 /ሃያ አምስት ሺህ ብር/ ብቻ፣ ለተሸከርካሪ ጎማ 18,000 /አስራ ስምንት ሺህ ብር/ ብቻ፣ ለግንባታ እቃዎች 25,000 /ሃያ አምስት ሽህ ብር ብቻ/ ፣ ለፅዳት ዕቃዎች 8,000 /ስምንት ሺህ ብር/ ብቻ በባንክ በተረጋገጠ የክፍያ ትዕዛዝ /ሲ.ፒ.አ/ ወይም በሁኔታ ላይ ያልተመሰረተ የባንክ ዋስትና ወይም በጥሬ ገንዘብ ማስያዝ አለባቸው፡፡
- ማንኛውም ተጫራች የጨረታ ሀሳቡን አንድ ወጥ በሆኑ ሁለት ቅጂዎች ማለትም ዋና/ኦሪጂናል እና ቅጂ/ኮር/ በማለት በጥንቃቄ በታሸገ ፖስታ በግ/ን/አስ/ቡድን ቢሮ ቁጥር 4 በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ዘወትር በስራ ሰዓት እስከ ቀን 08/03/ 2018 ዓ.ም ጠዋት 3፡30 ሰዓት ድረስ ማስገባት ይኖርባቸዋል፡፡
- ጨረታው ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በሀላፊ ክፍል ቢሮ ቁጥር 1 በ08.03/2018 ዓ.ም ጠዋት 4፡00 ሰዓት ይከፈታል።
- ተጫራቹ የዕቃውን ዝርዝር መግለጫ /እስፔስኬሽን / በማሟላት ዕቃው የተመረተበትን አገር የአምራቹን ስም፣ የዕቃውን ሞዴልና የመሳሰሉትን አካቶ መሙላት ይጠበቅበታል፡፡
- ውድድሩ በሎት ድምር ዋጋ ወይም በነጠላ ዋጋ ሊሆን ይችላል፡፡
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ስለ ጨረታው ዝርዝር መረጃ ከፈለጉ ቢሮ ቁጥር 4 ድረስ በአካል በመገኘት ወይም በስልክ ቁጥር 0224720080 በመደወል መረጃ ማግኘት ይችላሉ፡፡
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
የበረኸት ወረዳ ገንዘብ ጽ/ቤት
