Tender Detail

Tender Details

  • Company በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመልካሣ ግብርና ምርምር ማዕከል
  • Address መልካሣ : ኦሮሚያ ክልል ፡ ኢትዮጵያ, Phone: 0222250216
  • Website
  • Deadline21 Nov 2025, 12:00 AM
  • magazineአዲስ ዘመን
  • Bid Document Price1500.00
  • opening date2025-11-21 00:00:00
  • Categories Construction Works , Construction Works

በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመልካሣ ግብርና ምርምር ማዕከል የቢሮና ላብራቶሪ ሕንፃ የግንባታ ሥራ ለማከናወን ማዕከሉ የሚያስፈልጉ ግባዓቶችን በማቅረብ የባለሙያ የእጅ ዋጋ (Labor cost) በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡


ግልፅ የጨረታ ማስታወቂያ

በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመልካሣ ግብርና ምርምር ማዕከል የቢሮና ላብራቶሪ ሕንፃ የግንባታ ሥራ ለማከናወን ማዕከሉ የሚያስፈልጉ ግባዓቶችን በማቅረብ የባለሙያ የእጅ ዋጋ (Labor cost) በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ማሰራት ይፈልጋል፡፡

ስለዚህ ተጫራቾች፡-

1. በጨረታው ለመሳተፍ በዘርፉ የዘመኑን የታደሰ የንግድ ሥራ ፈቃድና የንግድ ምዝገባ የምስከር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡

2. የተጨማሪ እሴት ታክስ የምዝገባ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ:፡፡

3. የግብር ከፋይ ምዝገባ ሰርተፍኬት ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡

4.ተጫራቾች በጨረታው ለመሳተፍ ደረጃ 4 እና ከዚያ በላይ ያሉ G.C እና B.C የሥራ ተቋራጭ የሆኑ የግንባታ ሥራ ፍቃድ ያላቸው እና የታደሰ ብቃት ማረጋገጫ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችሉ፡፡

5. ከኢትዮጵያ ፌዴራላዊ ዲሞክራሲያዊ ሪፐብሊከ ከኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን 2017 በጀት ዓመት የግብር ግዴታቸውን የተወጡና 2018 በጀት ዓመት በጨረታ ለመሳተፍ የሚያስችል ማስረጃ ማቅረብ የሚችሉ ፡፡

ተጫራቾች በጨረታ ለመሳተፍ ከላይ ከተራ ቁጥር 1 እስከ 5 የተጠቀሱትን ማስረጃዎች ዋናውንና ኮፒ ከመጫረቻ ሰነዶቻቸው ጋር አያይዘው ማቅረብ አለባቸው፡፡

ተጫራቾች ማዕከሉ ለማሰራት የፈለገውን የግንባታ ዲዛይን ከጨረታ ሰነዱ ላይ ማግኘት ይችላሉ፡፡

ተጫራቾች ይህ ማስታወቂያ በጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ 20 (ሃያ)ተከታታይ ቀናት ዘወትር በሥራ ሰዓት ከሰኞ እስከ አርብ ከጠዋቱ 200 ሰዓት እስከ 600 ሰዓት ከሰዓት በኋላ 700 ሰዓት እስከ 1030 ሰዓት ድረስ ለጨረታ ማስከበሪያ ብር 50,000.00 /ሃምሳ ሺህ ብር/ በባንክ የተመሰከረ CPO ብቻ በማስያዝ የተዘጋጀውን የጨረታ ሰነድ ከአዳማ ከተማ ወደ አሰላ ከተማ በሚወስደው መንገድ 17 . በሚገኘው መልካሣ ግብርና ምርምር ማዕከል ከግዥና ፋይናንስ ሥራ አስፈፃሚ ቢሮ የማይመለስ ብር1,500 (አንድ ሺህ አምስት መቶ ብር) በመግዛትና የመወዳደሪያ ዋጋቸውን በመሙላት በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ መልካሳ ግብርና ምርምር ማዕከል ግልፅ ጨረታ . 03/2018 የመጫረቻ ሰነድ ዋና እና ቅጅ ተለይቶ በህግና ደንብ መሰረት ታሽጎ መግባት ይኖርበታል ፡፡

ጨረታው 20 ተከታታይ ቀናት ከፍት ሆኖ 20ኛው ቀን ከቀኑ 700 ሰዓት ታሽጎ በዚያው እለት ከቀኑ 730 ተጫራቾች ወይም ሕጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት በማዕከሉ መሰብሰቢያ አዳራሽ በግልፅ ይከፈታል ፡፡

ጨረታው የሚከፈትበት ዕለት የበዓላት ቀን ወይም ቅዳሜና እሑድ ከሆነ የጨረታው መከፈቻ ቀን በሚቀጥለው የሥራ ቀን ይዘዋወራል ፡፡

ዘግይተው የሚመጡ ሰነዶች ተቀባይነት የላቸውም፡፡

ማዕከሉ የተሻለ ዘዴ ካገኘ ጨረታውን ሙሉ በሙሉም ሆነ በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው፡፡

ለበለጠ መረጃ፡ -

በስልክ ቁጥር፡-+251222250216 የቢሮ እና 0911942650/0920947151 ደውለው መጠየቅ ይችላሉ፡፡

በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት የመልካሣ ግብርና ምርምር ማዕከል

በኢትዮጵያ የግብርና ምርምር ኢንስቲት

Save Tender