የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሲሲቲቪ ካሜራ በዋና ቅርንጫፍ ፅ/ቤት፣ በዞን ቢሮዎች እንዲሁም በፋርማሲዎች ላይ ማስተከል ይፈልጋል።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር አዲስ አበባ
ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
የሲሲቲቪ ካሜራ ለመግዛትና ለማስገጠም የወጣ ጨረታ ማስታወቂያ የኢትዮጵያ ቀደ መስቀል ማህበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት የሲሲቲቪ ካሜራ በዋና ቅርንጫፍ ፅ/ቤት፣ በዞን ቢሮዎች እንዲሁም በፋርማሲዎች ላይ ማስተከል ይፈልጋል።
- ሀ. ሎት-1 የሲሲቲቪ ካሜራ ግዥና ማስገጠም
በመሆኑም በጨረታዉ ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን መስፈርቶች ከጨረታ ሰነድ ጋር በማያያዝ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- በዘርፉ የተሰማሩ የዘመኑን የመንግስት ግብር የከፈሉ ወይም የ2017 ዓ.ም ንግድ ፍቃድ ያደሱ፣ በጨረታው መሳተፍ የሚያስችል ከገቢዎች ክሊራንስ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ የተመዘገቡበትን ማስረጃ እና የግብር መስያ ሰርተፍኬት ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ሰንዱ ተጫራች በሌላዉ ተጫራች ዋጋ ላይ ተንተርሶ መጫረት ከጨረታዉ የሚያሳግድ ይሆናል።
- ተጫራቾች ከጨረታው በኋላ የሚመስስ የጨረታ ማስከበሪያ ቢድ ቦንድ ለሚጫረቱበት ጠቅላላ ዋጋ ሁለት በመቶ (2%) በCPO ወደም ባንክ ጋራንቲ አያይዞ ማቅረብ ይኖርባቸዋል።
- ተጫራቾች የሚያቀርቡት ዋጋ ከተጨማሪ እሴት ታክስ ጋር መሆኑን ወይም አለመሆኑን መግለፅ ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራች ጨረታውን በሪፖርተር ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ባሉት ተከታታይ አስራ አምስት (15) የስራ ቀናት ውስጥ ጨረታ ሰነዱን በጉርድ ሾላ ሳሊህተ ምህረት ቤተክርስቲያን ፊት ለፊት ድራር ሞል አጠገብ ከሚገኘዉ ከኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማኀበር አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት በመገኘት የጨረታዉን ዝርዝር መረጃ የያዘውን የጨረታ ሰነድ በብር (800) ብር (ስምንት መቶ ብር) በመግዛት የጨረታ ሰነዳችሁን አስከ ሰኞ ህዳር 8/ 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ድረስ ለዚሁ በተዘጋጀው ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው።
- ተጫራች ጨረታውን አሸንፎ ባቀረበዉ ሰነድ መሰረት እቃዎቹን ሳያቀርብ ቢቀር ያስያዘዉ በባንክ የተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ድርጅቱ ገቢ ያደርጋል ወደም ተመሳሽ አይሆንም።
- ጨረታ ሰነዶችና ከጨረታዉ ጋር ተያያዥ የሆኑ ሰነዶች ማስትም ቴክኒካል ዋናውና ኮፒ እና ፋይናንሻል ዋናውና ኮፒ ዶክመንት በፖስታ በማሸገ ከጨረታ መዝጊያዉ ሰዓት በፊት ለዚህ በተዘጋጃዉ የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማሰገባት አለበት።
- ተጫራቾች የሚያቀርቧቸው ቁሳቁሶች አዲስ እና ጄኒውን መሆን ይጠበቅባቸዋል
- ቅርንጫፍ ጽ/ቤቱ ተጫራጮቾች የሚያቀርቡትን ዋጋ ሳይቀይሩ በትእዛዙ መጠን እስከ 25 በመቶ የመጨመር ወይም የመቀነስ መብት አለው።
- ጨረታው ሰኞ ህዳር 8/2017 ዓ.ም 8:00 ሰዓት ተዘግቶ በሰዓቱ 8:30 በጉርድ ሾላ በሚገኘዉ ሳሊህተ ምህረት ቤተክርስያን ፊት ለፊት ድራር ሞል አጠገብ በሚገኘዉ የማህበሩ መሰብሰቢያ አዳራሽ ውስጥ ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወክሎቻቸዉ በተገኙበት ይከፈታል፡፡
- አሸናፊው ተጫራች የጨረታው አሸናፊ መሆኑ ከተገለፀለት ወይም የጨረታ ውጤት ከተለጠፈበት ቀን ጀምሮ ምግብ ነክ እና ምግብ ነክ ያልሆኑ ቁሳቁሶችን ከ7ቀን ባልበለጠ ጊዜ ወይም በውሉ መሰረት ማቅረብ ይኖርበታል።
- ድርጅቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ተጫራቾች ስለጨረታዉ ተጨማሪ ማብራሪያ ሲፈልጉ ከዚህ በታች በተጠቀሰው አድራሻ ስልክ በመደወል ማግኘት የሚችሉ መሆኑን እንገልፃለን።
የኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር
አዲስ አበባ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
ስልክ ቁጥር: 011-515-06-08
ፖስታ ሳጥን ቁጥር: 41076
