ሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ለሥራ የሚፈልጋቸውን ሞተር ሳይክሎች /በነዳጅ የሚሠሩ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ/ በሁሉቱም አማራጮች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡
ለሁለተኛ ጊዜ የወጣ ግልጽ ጨረታ ማስታወቂያ
ሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን በ2018 በጀት ዓመት ኮርፖሬሽኑ ለሥራ የሚፈልጋቸውን ሞተር ሳይክሎች /በነዳጅ የሚሠሩ በኤሌክትሪክ የሚሠሩ/ በሁሉቱም አማራጮች በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም በዚህ ጨረታ መወዳደር የሚችሉ፡-
- ህጋዊ የንግድ ምዝገባ ፈቃድ ያላቸው፣
- በመስኩ የታደሰ የንግድ ፈቃድ ያላቸው፣
- የግብር ከፋይነት መለያ ቁጥር ያላቸው፣
- የቫት ተመዝጋቢነት ሰርተፊከት ያላቸው፣
- በአቅራቢነት ዝርዝር ውስጥ የተመዘገቡ መሆኑን የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ያላቸው ድርጅቶች ሀዋሳ ወንዶ ንግድ ኩባንያ ህንጻ ጀርባ በሚገኘው በኮርፖሬሽኑ ህንጻ 2ኛ ፎቅ ቢሮ ቁጥር 202 በአካል መምጣት የተዘጋጀውን ጨረታ ሰነድ የማይመለስ ብር 200 በመክፈል መግዛት ይኖርባቸዋል፡፡
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ 10,000 ብር በባንክ በተረጋገጠ CPO ብቻ ማስያዝ ይኖርባቸዋል።
- የጨረታውን የመወዳደሪያ ዋጋ ኮርፖሬሽኑ ባዘጋጀው ሰነድ ላይ በመሙላት ይህ የጨረታ ማስታወቂያ ከወጣበት ቀን ጀምሮ በ10 ተከታታይ ሥራ ቀናት ውስጥ የመወዳደሪያ ፖስታዎችን ቴክኒካል ኦሪጅናልና አንድ ኮፒ እንዲሁም ፋይናንሺያል ኦሪጅናልና አንድ ኮፒ እያንዳንዳቸውን ለየብቻ በሰም በታሸገ ኤንቬሎፕ በማድረግ በአንድ ትልቅ ፖስታ በማሸግ ለዚህ በተዘጋጀው የጨረታ ሳጥን ውስጥ ማስገባት አለባቸው፡፡
- ጨረታው በ11ኛው ቀን ከቀኑ 4፡00 ሰዓት ተዘግቶ በ4፡30 ሰዓት የሚከፈት ሲሆን ቀኑ የዕረፍት ቀን ወይም የበዓል ቀን ሲሆን በቀጣዩ ቀን በተመሳሳይ ቦታና ሰዓት ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል፡፡
መሥሪያ ቤቱ የተሻለ መንገድ ካገኘ ጨረታውን በከፊልም ሆነ ሙሉ በሙሉ የመሠረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
ለበለጠ መረጃ በስልክ ቁጥር፡- 09-16-03-72-61 ደውሎ መጠየቅ የሚቻል መሆኑን እንገልጻለን፡፡
የሲዳማ ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬሽን
