የሲዳማ ብ/ክ/መንግስት በ2018 ዓ/ም ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተዘርዘሩ ዕቃዎችን፡ ከተራ ቁጥር 1-4 የተዘርዘሩ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ግልጽ የጨረታ ማስታወቂያ
የሲዳማ ብ/ክ/መንግስት በ2018 ዓ/ም ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን ለቢሮ አገልግሎት የሚውሉ ከዚህ በታች የተዘርዘሩ ዕቃዎችን፡
|
ተ.ቁ |
የእቃው አይነት |
|
1 |
ሎት 1 እስቴሽነሪ እና የጽዳት ዕቃዎች |
|
2 |
ሎት 2 የኤሌክትሮኒክስ ዕቃዎች |
|
3 |
ሎት 3 የፈርኒቸር ዕቃዎች |
ከተራ ቁጥር 1-4 የተዘርዘሩ ዕቃዎችን በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ መግዛት ይፈልጋል።
ስለዚህ በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች፡-
- በዘርፉ የታደሰ ፈቃድ ያለው፡፡
- ለአቅራቢነት የሚያረጋግጥ የምስክር ወረቀት ማቅረብ የሚችል።
- ተጨማሪ እሴት ታክስ/VAT/ተመዝጋቢ የሆነ።
- የግብር ከፋይነት ሰርተፍኬትና መለያ ቁጥር ያለው።
- የዘመኑን ግብር ስለመከፈላቸው የግብር ከፋይነት ማስረጃ የሚያቀርብ።
- የሚገዙ ዕቃዎች ዓይነትና ዝርዝር ለእያንዳንዳቸው የጨረታ ሰነድ የማይመለስ 200/ሁለት መቶ ብር/ከፍሎ መግዛት አለባቸው።
- ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ ዋስትና ለሚወዳደሩበት የዕቃውን አይነት ለእያንዳንዳቸው ጠቅላላ ዋጋ 20,000 በባንክ በተረጋገጠ ሲፒኦ (CPO) ብቻ ማስያዝ አለበት።
- ተጫራቾች የጨረታ ሰነዳውን 1 ኦርጅናል ፋይናንሻል እና የቴክኒካል በ2 ኮፒ ለእያንዳንዳቸው በአንድ እናት ፖስታ በሰም በታሸገ ኤንቨሎፕ በማሸግ ማቅረብ አለባቸው።
- ጨረታው በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ከወጣበት ቀን ጀምሮ ለ15 ተከታታይ የሥራ ቀናት አየር ላይ የሚውል ሲሆን በ16ኛው ቀን ከጠዋቱ 4፡00 ሰዓት ላይ ታሽጎ በዚያው ዕለት 8፡30 ሰዓት በሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ልማት ባለስልጣን ግዥ ፋ/ን/አስ/ዳይሬክቶሬት ክፍል ቢሮ ቁጥር 02 ተጫራቾች ወይም ህጋዊ ወኪሎቻቸው በተገኙበት ይከፈታል።
- መ/ቤቱ የተሻለ አማራጭ ካገኘ ጨረታውን በሙሉ ወይም በከፊል የመሰረዝ መብቱ የተጠበቀ ነው።
- በጨረታው ለመሳተፍ የሚፈልጉ ተጫራቾች ተጨማሪ መረጃ ቢያስፈልጋቸው ግዥ ፋ/ን/አስ/ዳይሬክቶሬት በስልክ ቁጥር፡- 046 212 2897 በመደወል ማግኘት ይችላሉ።
የሲዳማ ብ/ክ/መንግስት ቡና፣ ፍራፍሬና ቅመማ ቅመም ባለስልጣን
